1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ህዝባቸውን ለመመገብ አስጊ ሁኔታ ላይ ያሉ ሀገራት

ረቡዕ፣ ነሐሴ 19 2002

ማፕልክሮፍት ያወጣው ደረጃ በምግብ እጥረት ሳቢያ ህዝባቸውን መመገብ የማይችሉ ካላቸው ውስጥ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ናቸው።

https://p.dw.com/p/Ow8r
ምስል picture alliance/dpa

ማፕልክሮፍት የተሰኘው የብሪታንያ የአየር ንብረት ተመራማሪ ድርጅት ፤ ለተባበሩት መንግሥታት የምግብ ድርጅት ፤ ስለምግብ ዋስትና ባደረገው ጥናት ፤ ህዝባቸውን በሚገባ መመገብ የሚችሉትን አገሮችና በምግብ እጥረት ለአደጋ ሊጋለጡ የሚችሉትን ዝርዝር በማውጣት አስታውቋል። በጥናቱ መሠረት ፤ የሰሜን አሜሪካ አገሮች፤ ከአውሮፓም ፤ ፊንላንድ፤ እስዊድን፣ ኖርዌይና ደንማርክ ላቅ ያለውን ደረጃ ይዘዋል። ከዚህ አንጻር፤ በሰላም ማጣት የምትታመሰው አፍጋኒስታንና በተለይ 9 የአፍሪቃ አገሮች፤ በከፍተኛ የምግብ እጥረት ሳቢያ፤ ህዝባቸውን ለመመገብ እንደሚሳናቸውና አሥጊ ደረጃም ላይ እንደሚገኙ ሠንጠረዡ ያስረዳል።

ድልነሣ ጌታነህ

መሳይ መኮንን

አርያም ተክሌ