1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ለሕጻናት በቂ የተመጣጠነ ምግብ UNICEF

ሐሙስ፣ ኅዳር 16 2008

ባለፈዉ የበልግ እና የክረምት ወራት በተከሰተዉ የዝናብ እጥረት ምክንያት በከፊል ትግራይ፤ ኦሮሚያ በአፋር እና በሶማሌ ክልሎች ለድርቅ መጋለጣቸዉ በይፋ ተነግሯል።

https://p.dw.com/p/1HD4j
UNICEF verliert laut Medienberichten das Spendensiegel des DZI
ምስል AP

[No title]

በአሁኑ ጊዜ ድርቁ እየከፋ በመሄዱ የተባበሩት መንግሥታት የተለያዩ ድርጅቶች ለድርቅ ተጎጂዎች ተገቢዉ ርዳታ እንዲደርስ የየበኩላቸዉን ግዳጅ ለመወጣት እየሠሩ እንደሚገኙ የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ በላከዉ ዘገባ ጠቅሷል። ድርጅቶቹ በተቀናጀ መንገድ በቅርቡ በጋራ ጉዳዩን አስመልክተዉ የጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ ይጠበቃል። እንዲያም ሆኖ የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት አድን ድርጅት በእንግሊዝኛ ምህፃሩ UNICEF በየትኛዉ ስፍራ ድርቅ ሲከሰት ፈጥነዉ ለጉዳት ለሚዳረጉት ሕጻናት በቂ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት እንዳለዉ አመልክቷል። ጌታቸዉ የድርጅቱን ኃላፊ በማነጋገር ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።

ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

ሸዋዬ ለገሠ

አርያም ተክሌ