1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሕፃናት ወታደሮች በአፍሪቃ

ረቡዕ፣ የካቲት 6 2005

ህፃናት ለወታደርነት እንዳይመለመሉ ለማከላከል የተጀመረዉ ዘመቻ ዘንድሮም በዛሬዉ ዕለት ታስቦ ዉሏል። "Red Hand Day" በመባል የሚካሄደዉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ሲከበር ዘንድሮ ለ11ኛ ጊዜ ነዉ።

https://p.dw.com/p/17d02
Unicef kündigt Aktion gegen Kleinwaffen an. Ein zwöfjähriger Kindersoldat in der Stadt Bo in Sierra Leone präsentiert seine Kalaschnikow. Vor dem Weltkindertag am 20. September hat das Kinderhilfswerks terre des hommes darauf hingewiesen, dass immer mehr Kinder weltweit Opfer von Gewalt werden. Sie griffen auch selbst zur Waffe, um ihre Überlebenschancen zu wahren, sagte die Vorsitzende des Kinderhilfswerks, Boxler. Die Verfügbarkeit von weltweit etwa 125 Millionen automatischer Kleinwaffen wie Maschinengewehre oder Handgranaten heize die Situation an. In diesem Zusammenhang kündigte das deutsche UNICEF- Komitee zum Weltkindertag eine Aktion "Stoppt Kleinwaffen" an.
ምስል picture-alliance/dpa

 በዚህ ወቅትም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች እና ህፃናት ላይ የሚያተኩሩ ግብረሰናይ ድርጅቶች ልጆች በጦር መሳሪያ ግጭት እንዳይሳተፉ የሚያቀርቡትን ተቃዉሞ የዓለም ህዝብ እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል። አፍሪቃ ዉስጥ ልጆች የጦርነትና የጥቃት ሰለባ መሆናቸዉ እንደቀጠለ፤ አማፂ ቡድኖችና የመንግስታት ሠራዊትም ለየራሳቸዉ ዓላማ እንደሚጠቀሙባቸዉ ተገልጿል።
ሱዳን፤ ደቡብ ሱዳን፤ ሲማሊያ፤ ቻድ፤ ልጆች በእርስ በርስ ጦርነት በግድ እንዲሳተፉ ከተደረገባቸዉ የአፍሪቃ ሀገራት ጥቂቶቹ ናቸዉ። በአሁኑ ወቅት ደግሞ ማሊ ለየት ያለ ስጋት አስከትላለች። ዓለም ዓቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት ሂዉመን ራይትስ ዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ታዳጊ ሕፃናት በፅንፈኛዉ እስላማዊዉ ቡድን ተገደዉ ለዉጊያ ሳይሰለፉ እንዳልቀሩ ያምናል። የድርጅቱ የምዕራብ አፍሪቃ ፅህፈት ቤት የበላይ ኮሪነ ዱፍካ ሰሜን ማሊ ዉስጥ ጉዳዩ ከሚመለከታቸዉ ወገኖች ጋ ካደረጉት ንግግር በመነሳት በአካባቢዉ ያለዉን ሁኔታ እንዲህ ይገልፃሉ፤
«አብዛኞቹ ልጆች ለዚህ ጉዳይ ገንዘብ እየተከፈላቸዉ ህፃናትን ለዚህ ተግባር በሚመለምሉ ትላልቅ ሰዎች አማካኝነት ነዉ ለታጣቂዉ ቡድን የሚወሰዱት። አክራሪ ሙስሊሞቹ ምልመላዉን ለረዥም ጊዜ በወግ አጥባቂነት በመንደሩ በታወቁ ሰዎች ላይ የጣሉት ይመስላል።»  
እሳቸዉ እንደሚሉትም ታጣቂዎቹ እነዚህን ልጆች በተኩስ ልዉዉጡ ግንባር የሚያሰልፉበት አጋጣሚ አለ። የአይን ምስክሮችም የፈረንሳይ ወታደሮች ጋኦ ከተማ በሚገኘዉ የአማፂያን ጦርሰፈር ላይ ጥቃት ከመሰንዘራቸዉ አስቀድሞ ልጆቹን እዚያ መመልከታቸዉን ይናገራሉ። የታዳጊዎቹ እጣፈንታም ምን እንደሆነ እስከአሁን የታወቀ ነገር የለም።  
«ስለዚህ ልጆቹ ከታጣቂ ሙስሊሞቹ ጋ እንዲሸሹ ተደርገዉ ይሁን፤ ወይም እንዲመለሱ ተደርጎ ይሁን ማወቅ አልቻልንም። አንዳንድ ወላጆች የሸሹት ታጣቂዎቹ ልጆቻቸዉን እንዲለቁላቸዉ ተማፅኖ አቅርበዋል። ልጆቹ ምን እንደደረሰባቸዉ እንግዲህ በቀጣይ መከታተልና ማጣራት ይኖርብናል።»   
ምንም እንኳን ልጆቹ ከዚህ ግርግር የማምለጥ እድሉ ቢኖራቸዉም ያለፉት የህይወት አጋጣሚ የሚያሳድርባቸዉ ተፅዕኖ ቀላል እንደማይሆን ነዉ የሚታመነዉ። በአንድ ወቅት በልጅ ወታደርነት ተሰማርተዉ የቆዩት ታዳጊዎች የስነልቡና ጉዳት ብቻ ሳይሆን በእድሜያቸዉ ሊያገኙት የሚገባዉን ትምህርትና ስልጠና ሁሉ ባለማግኘታቸዉ ይቸገራሉ። ኤሪክ ሞንጎ ዴሞክራቲክ ሪፑብሊክ ኮንጎ ይህን አስተዉለዋል። የኮንጎ ሰሜናዊ ግዛት ኢቱሪ ክፍለ ሀገር ደም አፋሳሹን የእርስ በእርስ ጦርነት ለአስር ዓመት አስተናግዳለች። ሞንጎ የሚመሩት ህፃናትን የሚረዳዉ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት «አፊያ» ከጦር ግንባር የተመለሡ የልጅ ወታደሮችን ይንከባከባል። ሆኖም የሚደረገዉ በቂ አይደለም ነዉ የሚሉት፤
«ድርጅቱ የቀድሞ ጥፋተኞችን በሚያስተናግድበት ሂደት አድ ያስተዋለዉ ነገር አለ። ይኸዉም ልጆቹን እንዲቀበልና እንዲዋሃዱ እንዲረዳቸዉ ከማኅበረሰቡ ጋ በዚህ ጉዳይ ላይ በጋራ መስራት ይኖርብናል።»
እሳቸዉ የሚመሩት ድርጅት ሥራ ከጀመረ ከዛሬ ሶስት ዓመት አንስቶ እስካሁን 520 ልጆችን በአግባቡ እየተንከባከበ ይገኛል። «መብትና ሰላም» በተሰኘዉ ትስስር አካልነቱም ዓለም ዓቀፍ  የጦር ወንጀል ችሎት ለጉዳት ሰለባዎች በዘረጋዉ የገንዘብ ርዳታ ተቋም ይደገፋል። የዛሬ አስር ዓመት የተቋቋመዉ የገንዘብ ተቋም ለጦርነት ሰለባዎች የሚዉል ወደ1,2 ሚሊዮን ዮሮ የሚገመት ካሳ መድቧል። ፍርድ ቤቱ ባለፈዉ ዓመት ነሐሴ ወር ለመጀመሪያ ጊዜ በኮንጎ አማፂ ቡድን መሪ ቶማስ ሉባንጋ ሥር እንዲሰለፉ ለተገደዱ ልጆች ካሳ እንዲሰጥ ወስኗል። ሆኖም ገንዘቡ ለአማፂ ቡድኖች ዓላማ በጦር ግንባር እንዲዉሉ የተገደዱ ልጆችን ሁሉ ለመርዳት በቂ እንዳልሆነ ነዉ የተገለፀዉ። ዛሬም ከአስር ዓመታት በኋላ በኮንጎዋ ኢቱሪ የሚታየዉ ሁኔታም ለወጣቶቹ የጦርነት ሰለባዎች ገና ብዙ መሰራት የሚገባዉ ነገር እንዳለ ያመለክታል። 

Afrika Goma Kongo Kindersoldaten Resozialisierung
ምስል © UNICEF/NYHQ2011-0351/Asselin
Demokratische Republik Kongo Wahl Wahlen 2011 Kindersoldaten Kindersoldat
ምስል picture alliance/dpa

 ፊሊፕ ዛንድነር

 ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ