1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሙርሲ እና የግብፅ የቱሪዝም ዘርፍ

ረቡዕ፣ ሰኔ 27 2004

ከግብፅ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ በኋላ የሀገሪቱ የቱሪዝም ዘርፍ ስጋት አድሮበታል። ከየስድስቱ የግብፅ የስራ ቦታ መካከል አንዱ ብዙ ቱሪስቶች ወደፊትም ሀገሪቱን በሚገበኙበት ድርጊት ላይ ጥገኛ ነው።

https://p.dw.com/p/15RGG
epa02484251 General view of the beach at the Red Sea resort of Sharm el Sheik, Egypt, 07 December 2010. A German tourist has been killed after a shark attack in the Red Sea off Sharm el-Sheikh, Egypt on 05 December 2010, Egyptian officials have subsequently imposed a 72-hour swimming ban in part of the area, one of Egypt's most popular tourist destinations. EPA/KHALED EL FIQI
ምስል picture-alliance/dpa


አዲሱ የሀገሪቱ መንግሥት ለምሳሌ አለባበስን ወይም የአልክሆል መጠጥን በተመለከተ ሊያሳርፈው የሚችል ገደብን፡ ቱሪስቶችን ሊያስደነግጥ ስለሚችል፡ መሥሪያ ቤቱ እንደማይቀበለው አስታውቀዋል።
በግብፅ የቀይ ባህር ዳርቻ በምትገኘዋ የኤል ጉና ከተማ የሚኖሩት የጥልቀት ዋና መምህር የ 36 ዓመቱ ኤክራሚ ላቲፍ ሞሀመድ ሙርሲ ፕሬዚደንት ሆነው መመረጣቸው በይፋ በተነገረበት ዕለት ከሁለት ጥሩምባ እየነፉ ከተንቀሳቀሱ መኪኖች በስተቀር በከተማይቱ ፅጥታ ሰፍኖ እንደነበር ያስታውሳሉ፤ ምክንያቱም ብዙዎቹ የከተማይቱ መራጮች ድምፃቸውን የሰጡት ለሙርሲ ተፎካካሪና የቀድሞው መንግሥት ተወካይ ለአህመድ ሻፊቅ ነበር። በቱሪዝም የሚተዳደሩት የኤል ጉና ነዋሪዎች ሀገር ጎብኚዎቹ ከከተማይቱ እንዳይርቁ መስጋታቸውን ኤክራሚ ገልጸዋል።
« አዎ በርግጥ ሙርሲን እፈራለሁ። ቱሪስቶቹ ተመሳሳይ የአየር ፀባይ ወዳላት፡ ግን ይበልጥ እንግዳ ተቀባይ ወደሆነች ሌላ ሀገር ይሄዳሉ ብየ የስባለሁ። »

ኤል ጉና እንግዳ ተቃባይነት አይጎድላትም። ቱሪስቶች የሚዝናኑባት የተለያየ የውኃ ስፖርት የሚያካሂዱባት ተስማማ አየር ያላት ከተማ ናት። ግን፡ ይህ ሁሉ በቅርቡ ያከትምለታል ብለው ነው የሚያስቡት፤ ምክንያቱም አንዳንድ ከጥቂት ሣምንታት በፊት በተበተነው ምክር ቤት የተወከሉ የሙሥሊም ወንድማማችነት እንደራሴዎች ብዙ ሰውነት የሚያሳየውን የዋና ልብስ፡ ቢኪኒ እና የአልክሆል መጠጥ እንዲከለከል ሲወያዩ ነበር። ይህ ዕቅዳቸው ገሀድ ሆኖ ቢሆን ኖሮ ለኤል ጉና እና ሌል ቱሪስት መስህብ ለሆኑ ከተሞጭ ሁሉ ውድቀት በሆነ ነበር። ቱሪዝም በብፅ ኤኮኖሚ ሦስተኛው ዋነኛ ምሰሶ እንደመሆኑ መጠን፡ የቱሪስቶች ቁጥር የሚቀንስበት ሁኔታ የወደቀውን የሀገሪቱን ኤኮኖሚ ይበልጡን ይጎዳዋል።
በግብፅ አራት ጊዜ ዕረፍትዋን ያሳለፈችው የኔዘርላንድስ ዜጋ የሆነችው አነማሪ ቤከር ወደፊት ወደ ግብፅ ስትሄድ ምንም ዓይነት ገደብ እንዲያርፍባት እንደማትፈልግ ነው የገለጸችው።
« ቢኪኒ መልበስ ወይም አልክሆል መጠጥ መጠጣት ካልቻልኩ ተመልሼ አልመጣም። ግን፡ እዚህ ደስ ይለኛል። ይህ ገደብ ግን ከልክ ያለፈ ነው። »«
በወቅቱ እንደሚታየው ግን፡ ይህ ዓይነቱ ገደብ የሚያርፍ አይመስልም። የቱሪዝሙ ዘርፍ ለሀገራቸው ምን ያህል አስፈላጊ መሆኑን በሚገባ የሚያውቁት አዲሱ ፕሬዚደንት ሙርሲ ባለፈው የሣምንት መጨረሻ ሥልጣናቸውን በይፋ በተረከቡበት ጊዜ ባሰሙት ንግግራቸው የቱሪዝሙ ዘርፍ ከሕዝባዊው ዓብዮት በፊት እንደነበረው ለማጣናከር የሚቻላቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። በግብፅ ቱሪዝም ሚንስቴር ዘገባ መሠረት፡ ሀገሪቱ በ 2011ዓም ከዚሁ ዘርፍ ያገኘችው ገቢ በ 20101 ዓም ከነበረው 30 ከመቶ ቀንሶዋል። እና በመዲናይቱ ካይሮ ሁከት በተነሳ ቁጥር፡ ምንም እንኳን መዲናይቱየቱሪስት መስህብ ከሆኑት የባህር ዳር ከተሞች ብዙ ብትርቅም እና ኤል ጉናን የመሳሰሉት ከተሞች ከካይሮ በጣም የተለዩ ቢሆኑም፡ ቱሪስቶች ከሀገሪቱ እንደሚርቁ ነው የታየው።
ያም ቢሆን ግን፡ አዲሱ ፕሬዚደንት ቃላቸውን እንደሚጠብቁ በኤል ጉና የቱሪዝም መሥሪያ ቤት ተጠሪ አድሃም ማህሙድ እምነቱን ገልጾዋል። ሙርሲ ሥልጣን ከያዙ ወዲህ በኤል ጉና አንድም ሀገር ጎብኙ ጉዞውን አልሰረዘም። እንደ አድሀም ማህሙድ አስተሳሰብ፡ ሙርሲ ከእሥላማዊው ቀነኖ የበለጠ ትኩረሊሰጡት የሚገባ ብዙ ጉዳይ አለ።
« በመዘርዝሩ መጀመሪያ ላይ ስራ አጥነት፡ ድህነት እና ወዘተ ስታገኝ፡ እርግጠኛ ነኝ በሚገባ የሚንቀሳቀስ ኤኮኖሚን ልትነካ አትፈልግም፡ እንዲያውም ተጨማሪ ውጤት ላማግኘት ነው የምትፈልገው። »
የጥልቀት ዋና መምህሩ ኤራሚ ላቲፍ ግን እንደ ማህሙድ ብሩሕ አመለካከት የላቸውም። ፕሬዚደንት ሙርሲ ፖሊሲውን እንደወቅታዊው ሁኔታ የሚቀያይረው የሙሥሊም ወንድማማችነት አባል እንደመሆናቸው መጠን፡ ከአክራሪ ዎች ግፊት ቢያርፍባቸው ለቱሪስቶች የማይመቹ ሕጎችን ሊያወጡ ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳላቸው አስታውቀዋል። ግማሹ የኤል ጉና ሕዝብ ልክ እንደ ላቲፍ የክርስትና እምነት ተከታይ ሲሆኑ፡ እስከዛሬ ክርስትያንና ሙሥሊም በሰላም ጎን ለጎን ይየሚኖሩበት ሁኔታም ይቀየር ይሆን በሚል ላቲፍ መስጋታቸው አልቀረም።
« በክርስትና እምነት ተከታዮች አንፃር ብዙ ሕጎችች፡ አብያተ ክርስትያን መገንባትን ወይም ክርስትያንና ሙሥሊሞች እንዲለያኡ የሚያዙ ደንቦች ይወጣሉ ብየ አስባለሁ። የምናውቀው ነገር የለም፡ ግን ፈርተናል። »
እንግዲህ ሁሉ ነገር ጥገኛ የሚሆነው ሙርሲ ቃላቸውን በተግባር በሚተረጉሙበት ሂደት ላይ ይሆናል።

Im Süden fühlen sich Touristen sicherer im Vergleich zum Norden. Das Bild wurde am 03.03.12 in Luxor, Ägypten aufgenommen.  *** Copyright Abderrahmane Ammar, DW-arabic
ምስል DW
25/06/12 11:42:24 1929x2800(446kb) Muslim Brotherhood's president-elect Mohamed Morsy speaks during his first televised address to the nation in Cairo Muslim Brotherhood's president-elect Mohamed Morsy speaks during his first televised address to the nation at the Egyptian Television headquarters in Cairo June 24, 2012. Morsy's victory in Egypt's presidential election takes the Muslim Brotherhood's long power struggle with the military into a new round that will be fought inside the institutions of state themselves and may force new compromises on the Islamists. Picture taken June 24, 2012. To match Analysis EGYPT-ELECTION/STRUGGLE/ REUTERS/Stringer (EGYPT - Tags: POLITICS ELECTIONS)
ምስል Reuters

ቪክቶርያ ክሌበር

አርያም ተክሌ

ሒሩት መለሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ