1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ማሊ እና የጋዎ ከተማ ነዋሪዎች ሥጋት

ረቡዕ፣ የካቲት 6 2005

በማሊ ያማፅያኑ የሙዣው ቡድን በትልቋ የሰሜን ማሊ ከተማ ጋዎ ባለፈው እሁድ ጥቃት ከሰነዘረ ወዲህ ከተማይቱ እንደገና አለመረጋጋት ሰፍኖበታል። እርግጥ፣ የማሊ እና የፈረንሣይ ጦር ኃይላት ከተማይቱን እንደተቆጣጠሩ ቢገኙም፡

https://p.dw.com/p/17dZg
TO GO WITH AFP STORY BY SERGE DANIEL - EXCLUSIVE IMAGES A picture taken on July 16, 2012 shows fighters of the Islamist group Movement for Oneness and Jihad in West Africa (MUJAO) sitting in the courtyard of the Islamist police station in Gao. A group of armed youths has arrived in Gao from Burkina Faso, joining hundreds of other young African recruits who have come to sign up with radical Islamists controlling the northern Mali town. The new batch of youths will join others from Senegal and Ivory Coast milling about in the scorching heat in the courtyard of a building the jihadists have made the headquarters of their Islamic-law-enforcing police. AFP PHOTO / ISSOUF SANOGO (Photo credit should read ISSOUF SANOGO/AFP/GettyImages)
ምስል Getty Images

የፈረንሣይ ጦር በማሊ በጀመረው ዘመቻ የጋዎን ከተማ ከፅንፈኛ ሙሥሊም ቡድኖች ባስለቀቀበት ጊዜ የታየው የፈንጠዝያ ስሜት አሁን በሥጋት ተተክቶዋል።

የሙዣው ቡድን ዓማፅያን ሰሞኑን ከማሊ ጦር ኃይል ጋ ብዙ ሰዓታት የፈጀ የተኩስ ልውውጥ እንዳካሄዱ የማሊ ጦር ኃይል ቃል አቀባይ አስታውቆዋል። ቃል አቀባዩ አክሎ እንዳስረዳው፡ የፈረንሣይ ጦር በሄሊኮፕተር ጥቃት ከሰነዘረ ካለፈው እሁድ ምሽት ወዲህ በኋላ የፈረንሣይ፡ የማሊ እና የቻድ ወታደሮች በሰሜን ማሊ የምትገኘዋን ትልቋን የጋዎ ከተማ ከሙዣው ዓማፅያን ለመከላከል እና ያማፅያኑን ግሥጋሤ ለመግታት በዚያ ተሠማርተዋል። ባንዳንድ የጋዎ ከተማ ሠፈሮች የሙዣዎ ዓማፅያን እንዳሉ ቢሰማም፡ ስለ ጋው ከተማ ጊዚያዊ ሁኔታ ለዶይቸ ቬለ ቃለ ምልልስ የሰጡት የከተማይቱ ከንቲባ ሳዱ ዲያሎ የዜናውን ትክክለኛነት ማረጋገጡ እንዳማይችሉ ገልጸዋል።
« አሸባሪዎቹ በከተማይቱ መኖራቸውን ላውቅም ሆነ ላረረጋግጥ አልችልም። ስለበርካታ አሸባሪዎች አይደለም እየተነጋገርን ያለነው። በከተማይቱ ጥቂቶች ምናልባት አንድ ወይም ሁለት የሚሆኑ ሊኖሩ ይችላሉ። ከዚያ ባለፈ ግን በከተማይቱ መደበኛው ኑሮ ቀጥሎዋል። አሸባሪዎቹን በተመለከተ ሕዝቡ መረጃ ይሰጠናል። »
ዓማፅያኑ ከሰነዘሩት ጥቃት በኋላ ትልቁ የከተማይቱ መደብር ተጨማሪ ጥቃት በመሥጋት ተዘግቶ ነበር። አንዱ የከተማይቱ ነዋሪ እንደገለጸው፡ ከፈረንሣይ ዘመቻ በኋላ ከከተማይቱ የሸሹት ፅንፈኞቹ ሙሥሊሞች እንደገና ተመልሰው ሕዝቡን እንዳያሸብሩ ሠግቶዋል።
« ፈርተናል። ፈርተናል። አድፍጠው ጥቃት እንዳይጥሉብን ሠግተናል። እነዚህ ሰዎች ምናልባት ሊመለሱ ይችሉ ይሆናል።»
የፈረንሣይ፡ የማሊ እና የቻድ ወታደሮች ወታደሮች ሕዝቡን ለማረጋጋት እና አሉ የሚባሉ አሸባሪዎችን ለማደን ጥረት መጀመራቸውን ከንቲባው ሳዱ ዲያሎ አስረድተዋል። ይሁንና፡ ዛሬ ከማሊ በወጡ ዘገባዎች መሠረት፡ የፈረንሣይ ጦር ዓማፅያኑ በከተማይቱ ማዕከል የብዙ ሰው ሕይወት ለማጥፋት በማሰብ ያጠመዱት 600 ኪሎ ፈንጂ የያዘ ቤት ውስጥ የተሰራ ቦምብ ማምከናቸውን ለፈረንሣውያኑ ዜና ወኪል አ ኤፍ ፔ ገልጸዋል። እንደሚታወሰው፡ በአንድ መቆጣጠሪያ ኬላ አንድ አጥፍቶ ጠፊ ጥቃት ጥሎ አንድ ወታደር ላቆሰለበት ድርጊት ቀደም ሲል የሙዣው ቡድን ኃላፊነቱን ወስዶዋል። የቡድኑ ቃል አቀባይ አቡ ዋሊድ ዛህራዊ ለፈረንሣይ ዜና ወኪል እንዳስታወቁት፡ ፈረንሣይ ባለፈው ጥር ወር በማሊ ዘመቻ እስከጀመረችበት ጊዜ ድረስ ተቆጣጥረዋት የነበረችውን የጋዎን ከተማ መልሰው መቆጣጠር እስከሚቻል ድረስ ውጊያው ይቀጥላል።
ይህ በዚህ እንዳለ፡ በምሕፃሩ አፊስማ በሚል መጠሪያ የሚታወቀውለማሊ ተልዕኮ ድጋፍ የሚሰጠው ዓለም አቀፉ ሠራዊት ወታደሮች ዛሬም ወደዚችው ሀገር መግባታቸውን ቀጥለዋል። የምዕራብ አፍሪቃ መንግሥታት የኤኮኖሚ ማህበረሰብ፡ በምሕፃሩ የኤኮዋስ ሠራዊትን የወከሉት የቤኒን፡ የኮት ዲቯር እና የሴኔጋል ጦር ኃይላት ሰሞኑን ማሊ ከገቡት መካከል ተቆጥረዋል። በማሊ መከላከያ ሚንስቴር መግለጫ መሠረት፡ እስከተያዘው የየካቲት ወር ማብቂያ ከ 5000 የሚበልጡ ወታደሮች በሀገሩ ይሠማራሉ። ከ 65 እስከ 70 ከመቶ የሚሆነው አሁን በዚያ እንደሚገኝ የአፊሲማ ቃል አቀባይ ኮሎኔል ያዎ አጁማኒ ገልጸዋል።
ሰሜናዊ ማሊን ተቆጣጥረው የነበሩት ፅንፈኞቹ ያማፅያን ቡድኖች ወደ መዲናይቱ ባማኮ የጀመሩትን ግሥጋሤ ለማስቆም በማሊ ፕሬዚደንት ዲያንኩንዳ ትራውሬ ጥሪ ባለፈው ጥር 11 በዚችው ሀገር የጦር ዘመቻ የጀመረችው ፈረንሣይ የፊታችን መጋቢት ወር ጦሯን ማውጣት ትፈልጋለች። በዚህም የተነሳ፡ የኤኮዋስን ጦር ኃይላት ዕዝ በተመድ ሥር ለማዋል ድርድሩ ተጀምሮዋል። ይሁን እንጂ፡ የዓለሙ መንግሥታት ድርጅት ምክትል ዋና ፀሐፊ ያን ኤሊያሰን እንደጠቀሱት፡ የማሊ መንግሥት የተመድን ሰላም አስጠባቂ ሠራዊት ወደ ሀገሩ ለማስገባት እያመነታ ነው።
ሂደቶች ይህን በመሰሉበት ባሁኑ ጊዜ በማሊ ጦር ውስጥ የሚታየው ክፍፍል እንዲያበቃ ከፍተኛ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ጥሪ አሰምተዋል። ባንድ በኩል በመፈንቅለ መንግሥት የተወገዱትን ፕሬዚደንት አማዱ ቱማኒ ቱሬን በሌላ ወገን ደግሞ የመፈንቅለ መንግሥቱ መሪዎች በሚደግፉት የጦር ቡድኖች መካከል ባለፈው ዓርብ ጥር ስምንት: 2013 በተካሄደው የተኩስ ልውውጥ ሁለት ወጣቶች ሲገደሉ ሌሎች በርካቶች ቆስለዋል።

Les marsouins du 2eme RIMA accompagnent les soldat Nigerien dans leurs patrouilles pedestre et en véhicule dans la ville de GAO. Ils rencontrent la population et recueillent des informations sur la vie du village.Un dtachement de Liaison et d'assistance armé par le 2eme RIMA au profit de la MISMA accompagne depuis Niamey des éléménts de l'armée Nigerienne venue à GAO participer à la sécurisation. Les Nigerien sont aussi accompagnés par des éléments des EFS qui les ont formés dans leur pays.
ምስል picture-alliance/CITYPRESS24
epa03575372 A photograph made available 09 February 2013 shows Malian soldiers patrolling the market in Gao, northern Mali, on 07 February 2013. Islamist rebels reportedly have fled the towns of Timbuktu and Gao after French President Francois Hollande launched a unliateral air strikes and troop deployments last month but officials said the rebels still controlled large swathes of countryside. They have rocketed French and Malian troops in Gao and laid mines and improvised explosive deives killing at least four Malian soldiers on the roads between major towns, media sources said. EPA/SEB CROZIER
ምስል picture-alliance/dpa

አርያም ተክሌ
ነጋሽ መሀመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ