1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ምክትል ጠ/ሚ ኃይለ -ማርያም ደሳለኝና ኢህአዴግ፣

ዓርብ፣ ነሐሴ 18 2004

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ባራካ ኦባማ አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝን ትናንት በስልክ አነጋግረዋቸዋል ። ኦባማ በዚሁ ወቅት አቶ ኃይለ ማርያም የኢትዮጵያ መንግሥት ለልማት ለዲሞክራሲ ና ለሰብአዊ መብቶች እንዲሁም ለአካባቢ አገራት ደህንነት የሚሰጠውን ድጋፍ እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል ።

https://p.dw.com/p/15wQy
Ethiopian state television announced on August 21, 2012 that Hailemariam Desalegn will be acting prime minister, after the death of Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi.
ምስል CC-BY-SA- World Economic Forum

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናሉ ተብለው ለሚጠበቁት ለአቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሥልጣን ለማስረከብ የሚካሄደው ፖለቲካዊ ዝግጅት ቀጥሏል ። የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ባራካ ኦባማ አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝን ትናንት በስልክ አነጋግረዋቸዋል ። ኦባማ በዚሁ ወቅት አቶ ኃይለ ማርያም የኢትዮጵያ መንግሥት ለልማት ለዲሞክራሲ ና ለሰብአዊ መብቶች እንዲሁም ለአካባቢ አገራት ደህንነት የሚሰጠውን ድጋፍ እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል ። አቶ ኃይለ ማርያም ከዚህ ሌላ ትናንት አዲስ አበባ ተገኝተው በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማቸውን ሃዘን የገለጹትን የሱዳንና የኬንያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ተቀብለው አነጋግረዋል ። የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ በረከት ስምዖን ከ 3 አመት በኋላ በኢትዮጵያ ምርጫ እስከሚካሄድ ድረስ አቶ ኃይለ ማርያም የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ሥልጣን እንደሚይዙና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚያካሂደው አስቸኳይ ጉባኤ ፣ በይፋ ቃለ መሃላ እንደሚፈፅሙ ማስታወቃቸው ይታወሳል ። የቀድሞው የውሃ መሐንዲስ አቶ ኃይለ ማርያም የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነቱንና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትርነቱን ሥልጣን ከያዙ ገና 2 አመት አልሞላቸውም ። ከዚያ በፊት የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች መስተዳድር ፕሬዝዳንት ነበሩ ። የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት እንደዘገበው አቶ ኃይለ ማርያም እምብዛም በፖለቲካው መስክ የሚታወቁ ሰው አይደሉም ። በሌላ በኩል በኢትዮጵያ በሞት ለተለዩት ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ብሔራዊው ሃዘን ዛሬም ቀጥሏል ። በብሔራዊ ቤተ መንግሥት በርካታ ሰዎች ሃዘናቸውን በመግለፅ ላይ ናቸው ።የኢትዮጵያ ጠ/ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በሞት መለዬት፣ አገሪቱ ወደምን አቅጣጫ እንድታመራ ያደርግ ይሆን? የሚል ጥያቄ በሰፊው በማነጋገር ላይ ስለመሆኑ ይነገራል። በተለይ ምዕራባውያን አገሮች ፣ የአቶ መለስ ህልፈተ ህይወት፤ ከፍተኛ የሥልጣን ሽኩቻ ያመጣል ፣ ባካባቢውም መረጋጋት ላይኖር ይችላል የሚለውን ሥጋታቸውን ማንፀባራቀቸው አልታበለም። የኢህሰዴግ መንግሥት በበኩሉ ሥጋቱ መሠረት የለውም ይላል። ከለንደን ድልነሣ ጌታነህ ፤ ስለ ምክትል ጠ/ሚንስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የሚከተለውን ዘገባ አጠናቅሮ ልኮልናል።

epa03307749 (FILE) A file photo dated 17 September 2011 shows Ephiopian Prime Minister Meles Zeinawi speaking during a join press conference with his Egyptian counterpart Essam Sharaf (not pictured), in Cairo, Egypt. Reports on 16 July 2012 state that Meles Zenawi was unable to attend the opening on 15 July of the African Union Summit being held in Ethiopia because of rumoured health concerns. The Ethiopian government declined to make a statement on the issue. EPA/KHALED ELFIQI /POOL *** Local Caption *** 50045673
ምስል picture-alliance/dpa

ድልነሳ ጌታነህ

ተክሌ የኋላ

ነጋሽ መሐመድ