1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሞምባሳ ውስጥ የተገደሉት መንፈሳዊ መሪ

ረቡዕ፣ ነሐሴ 23 2004

ኬንያ ውስጥ መንፈሳዊ መሪ ሼክ አቦድ ሮቦ መሐመድ ሰኞ ዕለት በጥይት ተመተው ከተገደሉ በኋላ በሞምባሳ ከተማ ግጭት መነሳቱ ተነግሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ይህ ግጭት እንዲያበቃ ጥሪ አድርገዋል።

https://p.dw.com/p/15zWl
FILE - In this photo of March 15 2000, controversial Muslim cleric Aboud Rogo is seen in in Nairobi High Court, Kenya, during his hearing on terrorism charges. Rogo has been shot dead at a beach in Mombasa according to local sources Monday Aug. 27 2012. Rogo was among three Kenyans whose assets were frozen by the US government over alleged links to terrorism. But the three Aboud Rogo, Abubaker Shariff Ahmed and Omar Awadh Omar denied the charges and challenged the US government to table evidence against them. The cleric was shot inside his car in front of his wife and children. Reports indicate that the wife was injured during the shooting and his 5 year old daughter was shot on her right leg.(Foto:Khalil Senosi, File/AP/dapd)
ሼክ አቦድ ሮቦ መሐመድምስል dapd

አመፅ የሚያስነሱት ካላቆሙምም ጠንካራ ርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስጠንቅቀዋል። ለሰብዓዊ መብት ተማጋች ድርጅት ሁማን ራይትስ ዎች በጉዳይ ላይ ያለውን ፤ ልደት አበበ እንደሚከተለው አሰባስባለች።

« አገሪቷን በጉልበተኛ ስርዓት አመራር ልናራምድ አንችልም ነው ያሉት፤ የኬንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ። አክለውም ግድያን ፍፁም አንፈቅድም ሲሉ ተናግረዋል። ሼክ አቦድ ሮጎ መሐመድ ያለፈው ሰኞ ባልታወቀ ሰው ከተገደሉ በኋላ ሞምባሳ ገና ዛሬ ነው የተረጋጋችው። የሁማን ራይትስ ዎች የምስራቅ አፍሪቃ ጉዳይ ተመራማሪ ቤን ሮውሌንስ እንደሚሉት፤ ጉዳዩ አሳሳቢ ነው።

Protesting Muslim youths stand next to burning tires in Mombasa, Kenya Monday Aug. 27, 2012 after Aboud Rogo, a Muslim cleric facing terror-related charges, was shot dead. Gunmen in Kenya's coastal city of Mombasa shot dead a Muslim cleric accused by Washington and the United Nations of supporting al-Qaida-linked militants in Somalia, sparking rioting by youths who burned at least one police car and stoned businesses. Human rights groups say the killing on Monday of Aboud Rogo falls into a pattern of extrajudicial killings and forced disappearances of suspected terrorists, allegedly being orchestrated by Kenyan police. (Foto:AP/dapd)
በተነፃው አመፅ መኪናዎች እሳት ተለኩሰዋል።ምስል dapd

« ማንም ይሁን ማን ድርጊቱን የፈፀመው አንዳንድ በነዚህ ሰዎች የተቆጡ ራሳቸውን በትጋት የሚከላከሉ ኬንያውያንም ይሁኑ የኬንያ ባልስልጣናት ድብቅ ኃይል በጉዳዩ ለመጨነቅ በቂ ምክንያት አላቸው።»

ከቤተሰባቸው ጋ ከሞምባሳ ወደ ማሊንዲ ሲጓዙ በጥይት ተመተው የተገደሉት መንፈሳዊ መሪ፤ ከአሸባብ ቡድን ጋ ግንኙነት አላቸው ተብሎ ይገመታል። ለቡድኑም ሶማሊያ ውስጥ ገንዘብ እና ተዋጊዎች አቅርበዋል በማለት ይተቻሉ። ዩናይትድ እስቴትስ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአሸባሪነት እቀባ ከተደረገባቸው ስም ዝርዝር ውስጥ ከተዋቸዋል። በርግጥ ከግድያው በስተጀርባ ስላለው ሰው እስካሁን የኬንያ መንግስትም ይሁን የሰው መብት ተሟጋጅ ድርጅቶች አልደረሱበትም። እንደ ኬንያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተጠባባቂ ምክትል ዋና ፀሀፊ ፤ በርንናርድ ሞጌሳ ገለፃ፤ ከሆነ የመንፈሳዊው መሪ ሼክ አቦድ ሮቦ መሐመድ የተገደሉት በፖሊስ ድክመት ነው።

« ህይወታቸው በአደጋ ላይ እንደሚገኝ አንድ ዘገባ እንኳን ከወጣ የፖሊስ ኃላፊነት ነበር ምን አይነት ሰው ተገቢው ጥበቃ ሊደረግለት እንደሚችል። ይህ የፖሊስ ቸልተኝነት ነው ማለት እችላለሁ። ወቀሳቸው በጥሞና አልተደመጠላቸውም። አንዳንድ ከለላ አልተሰጣቸውም።»

Kenyan police patrol the port city of Mombasa on August 27,2012 after riots following the killing of a radical cleric linked to Somalia's Al-Qaeda allied Shebab, Aboud Rogo Mohammed. One person was killed and two churches were looted in Mombasa on August 27, after the killing of the cleric. Thousands of angry protesters gathered following Mohammed's killing, blocking off streets around the mosque where he had often preached, setting fire to vehicles and chanting slogans in his support. AFP PHOTO / STRINGER (Photo credit should read -/AFP/GettyImages)
በአመፄ ቦታ የኬንያ ፖሊስምስል Getty Images

የመንፈሳዊ መሪው ደጋፊዎች ባስነሱት አመፅ ቤተ ክርስትያናት እና መኪናዎች በእሳት ተለኩሰዋል። ሱቆች መዝብረዋል። እንደ BBC ዘገባ ደግሞ አብያተ-ክርስቲያን ይህንን ድርጊት ለመቃወም ያደረጉትን ጥሪ ግጭቱን ይበልጥ ላለማጠናከር በሚል ሰርዘውታል። የኬንያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተጠባባቂ ምክትል ዋና ፀሀፊ ፤ ሞጌሳ ወደፊትም

እንደዚህ አይነት ድርጊቶችን ለመከላከል እንደ መፍትሄ የሚያዩትን ሲገልፁ፤

« ሁለት መፈፀም ያለብን ነገሮች አሉ። የመጀመሪያው ያካባቢው ባለስልጣናት ስለአካባቢው ሰላም አንስተው መወያየት ይኖርባቸዋል። ሁለተኛ ፖሊስ ከወንጀል ጋ የተያያዙ ድርጊቶችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ማሳየት አለበት። ሰዎች በፖሊስ አቅም መተማመን እንዲችሉ።»

በአቦድ ሮጎ ግድያ እስካሁን በቁጥጥር ጥር የዋለ አካል የለም። እንደ «ደይሊ ኔሽን» ዘገባ ከሆነ የመንፈሳዊ መሪው ደጋፊዎች ባስነሱት አመፅ 20 የሚደርሱ ሰዎች ታስረዋል።

ልደት አበበ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ