የኢትዮጵያ መንግሥት መግለጫ
ዓርብ፣ ሐምሌ 8 2008ማስታወቂያ
በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ በጎንደር ከተማ የተከሰተው ግጭት መብረዱን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ ። የኢትዮጵያ መንግሥት የክምኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ ለሃገር ውስጥ እና ለውጭ ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የፌደራል እና የክልል የፀጥታ ኃይላት ባደረጉት ርብርብ አካባቢው መረጋጋቱን ተናግረዋል ። አቶ ጌታቸው በመግለጫቸው እንዳሉት በግጭቱ የሰው ሕይወት ጠፍቷል ንብረትም ወድሟል። ጋዜጣዊ መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝሩን ልኮልናል ።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ