1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስኖውደን ተሸለመ

ሐሙስ፣ መስከረም 15 2007

ስኖደን የተሸለመዉ በዓለም የማትደፈረዉን ሐያል ሐገር በማጋለጥ ለመናገር ነፃነት መከበር መቆሙን በማረጋገጡ ነዉ።ለወትሮዉ የተሸላሚዎች ሥም ዝርዝር በይፋ የሚነገርበት የሲዊድን ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ግን መስሪያ ቤት ግን የዘንድሮ ተሸላሚዎች ስም ዝርዝር ከቢሮዉ እንዳይነገር አግዷል

https://p.dw.com/p/1DL33
ምስል picture-alliance/dpa

የዩናይትድ ስቴትስን መንግሥትን የሥለላ ሴራ በማጋለጡ ከሐገሩ ለመሰደድ የተገደደዉ የቀድሞዉ አሜሪካዊ የሥለላ ድርጅት ባልደረባ ኤድዋርድ ስኖደን «አማራጭ ኖቤል» የተሰኘዉን ሽልማት አገኘ።መንበሩን ስቶክሆልም-ስዊድን ያደረገዉ ሸላሚ ድርጅት RightsLivelihood እንዳስታወቀዉ ስኖደን የተሸለመዉ በዓለም የማትደፈረዉን ሐያል ሐገር በማጋለጥ ለመናገር ነፃነት መከበር መቆሙን በማረጋገጡ ነዉ።ለወትሮዉ የተሸላሚዎች ሥም ዝርዝር በይፋ የሚነገርበት የሲዊድን ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ግን መስሪያ ቤት ግን የዘንድሮ ተሸላሚዎች ስም ዝርዝር ከቢሮዉ እንዳይነገር አግዷል።

ቴዎድሮስ ምሕረቱ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ