ሶማሊያና ተመድ
ዓርብ፣ ሚያዝያ 13 2009ማስታወቂያ
የሶማሊያ መንግሥት የሐገሪቱን ፀጥታ ለማስከበር እና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ተባብሮ እየሠራ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።ድርጅቱ እንደሚለዉ ሶማሊያ ከዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ እና ከአካባቢዉ ማሕበራት ጋር የመሠረችዉ ትብብር የፀጥታ ኃይሏን ለማጠናከር፤ ረሐብን ለመከላከል፤ ሙስናን ለመዋጋት እና የመንግሥቱን መዋቅር ለማጎልበት ጠቃሚ ነዉ።የሶማሊያን ጉዳይ የሚከታተሉ አንድ የማሕበራዊ ጉዳይ ምሑር ግን የዓለም አቀፉን ድርጅት ተስፋ ብዙም አልተቀበሉትም።የዋሽንግተን ዲሲዉ ወኪላችን መክብብ ሸዋ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።
መክብብ ሸዋ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ