1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሶሪያ፥ ዩናይትድ ስቴትስና «ቀዩ መስመር»

ዓርብ፣ ነሐሴ 17 2005

ያኒንግ እንደሚያምኑት የአሜሪካ ጦር ሶሪያ ከዘመተ የደማስቆ መንግሥትን የምትደግፈዉ ኢራን አሜሪካኖች ነገር እንደፈለጓት ነዉ የምትቆጥረዉ።የእስራኤል ደሕንነትም ላደጋ መጋለጡ አይቀርም።«ከዚሕም በተጨማሪ» ይላሉ ያኒንግ አሜሪካኖች «ጣልቃ መግባት» መጀመሪያዉ እንጂ ፍፃሜዉ እንደማይታወቅ ካለፈዉ አስር ዓመት ልምዳቸዉ በቅጡ መማር አለባቸዉ።

https://p.dw.com/p/19VQx
People, affected by what activists say is nerve gas, are treated at a hospital in the Duma neighbourhood of Damascus August 21, 2013. Syrian activists accused President Bashar al-Assad's forces of launching a nerve gas attack on rebel-held districts near Damascus on Wednesday that they said killed more than 200 people. There was no immediate comment from Syrian authorities, who have denied using chemical weapons during the country's two-year conflict, and have accused rebels of using them, which the rebels deny. REUTERS/Bassam Khabieh (SYRIA - Tags: POLITICS CIVIL UNREST CONFLICT)
አማፂያኑ «በመርዝ ጋዝ ተጠቁ» ያሏቸዉምስል Reuters

የሶሪያ መንግሥትን ጦር ባለፈዉ ሮብ ርዕሠ-ከተማ ደማስቆ አካባቢ የሚገኝ የደፈጣ ተዋጊዎች ይዞታን በኬሚካዊ ጦር መሳሪያ ደብድቧል በማለት ተቃዋሚዎቹ እየወነጀሉ ነዉ።መንግሥት ዉንጀላዉን አስተባብሏል።ምዕራባዉያን ሐገራት ጉዳዩ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባለሙያዎች እንዲጣራ አበክረዉ እየገፋፉ ነዉ።የሶሪያ መንግሥት እንደተጠረጠረዉ መርዛማ ጋዝ ተኩሶ ከሆነ ዩናይትድ ስቴትስ ካንድ ዓመት በፊት ያስጠነቀቀችዉ «ቀይ መስመር» ተጣሰ ማለት ነዉ።በዚሕም ሰበብ ልዕለ-ሐያሊቱ ሐገር የሐይል እርምጃ እንድትወስድ ግፊት እየተደረገባት ነዉ።ዩናይትድ ስቴትስ ግን፥ ክርስቲያን ኢግናትሲ እንደዘገበዉ የሐይል እርምጃ ለመዉሰድ የተዘጋጀች አይመስልም።የኢግናትሲን ዘገባ ነጋሽ መሐመድ አጠናቅሮታል።

ፕሬዝዳት ባራክ ኦባማ ካንድ ዓመት በፊት «ቀይ መስመር» ያሉትን የማስጠንቀቂያ የሐሳብ ወሰን ማበጀታቸዉን ሲያዉጁ ብዙዎች የተረጎሙት፥ የሶሪያ መንግሥት ያን መስመር-በመርዛማ ጋዝ ፍንዳታ ከጣሰዉ፥ የዓለም ብቸኛ ልዕለ ሐያል ሐገር ሐያል ጦር የበሽር አል-አሰድን ሕልቅት ለመፈጥረቅ አያመነታም ብለዉ ነበር።

የሶሪያ መንግሥትን ለማስወገድ የሚፋለሙት ጠላቶቹ እንደሚሉት ባለፈዉ ሮብ የመንግሥት ጦር ደማስቆ አጠገብ በሚገኝ የአማፂያን ይዞታን በመርዛማ ጋዝ አጥቅቷል።በጥቃቱ ሲያንስ-አምስት መቶ ሲበዛ አንድ ሺሕ ሰወስት መቶ ሰዉ መገደሉ ተዘግቧል።የሶሪያ መንግሥት ዉንጀላዉን አስተብሏል።ዉንጀላዉ መርማሪዎች ከተረጋገጠ ግን ለበሽር አል-አሰድ አደገኛ ሊሆን ይችላል።

የዚያኑ ያክል ኦባማንም ጦር እንዲያዘምቱ ከሚፈልገዉ ሐይል ጠንካራ ግፊት የሚያጋልጥ ነዉ።ይሕ ግን የመጀመሪያ አይደለም።በገለልተኛ አጣሪዎች አልተረጋገጠም እንጂ የሶሪያ መንግሥት ባለፈዉ ሰኔ መርዛማዉ ጋዝ ተኩሶ የኦባማን «ቀይ መስመር» መጣሱን ራሳቸዉ አሜሪካኖች አስታዉቀዉ ነበር።

የኦባማ መስተዳድር ግን የሶሪያ አማፂያንን ለማስታጠቅ ወሰነ እንጂ ብዙዎች እንደፈሩት፥አማፂያኑና ደጋፊዎቻቸዉ እንደተመኙት ጦር አላዘመተም።በምሕፃሩ MDR የሚባለዉ የጀርመን ቴሌቪዥን ጣቢያ የዋሽግተን ወኪል ዚልከ ሐሰልማን እንደምትለዉ የኦባማ የዉጪ መሪሕ ከቡሽ የተለየ ነዉ።«ኦባማ» ጋዜጠኛዋ እንደምታምነዉ ልዕለ ሐያሊቱ ሐገራቸዉ በጦር ሐይል ጡንቻ ዓለምን የምታስገብር «የዓለም ፖሊስ» እድትሆን አይፈልጉም።የድርድር መፍትሔ የሚሹ መሪ ሆነዉ መታወስን እንጂ።

የጀርመን የዉጪ መርሕ ማሕበረሰብ ባልደረባ ዮሴፍ ያኒንግ እንደሚሉት ደግሞ ዩናይትድ ስቴትስ ሶሪያ ጦር የማታዘምተዉ አደገኛዉን መዘዝ ሥለምታዉቀዉ ነዉ።ያኒንግ እንደሚያምኑት የአሜሪካ ጦር ሶሪያ ከዘመተ የደማስቆ መንግሥትን የምትደግፈዉ ኢራን አሜሪካኖች ነገር እንደፈለጓት ነዉ የምትቆጥረዉ።የእስራኤል ደሕንነትም ላደጋ መጋለጡ አይቀርም።«ከዚሕም በተጨማሪ» ይላሉ ያኒንግ አሜሪካኖች «ጣልቃ መግባት» መጀመሪያዉ እንጂ ፍፃሜዉ እንደማይታወቅ ካለፈዉ አስር ዓመት ልምዳቸዉ በቅጡ መማር አለባቸዉ።

«ምክንያቱም በእንዲሕ ዓይነቱ ግጭት ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት ዉጤታማ ሊሆን እንደማይችል አሜሪካኖች ያዉቁታል።የአሜሪካ ጦር እንደዘመተ፥ እንዲዘምት ብቻ ሳይሆን ከዘመተበት ፈጥኖ እንዲወጣም አሜሪካኖች ላይ ወዲያዉ ግፊት ይደረግባቸዋል።»

በመሠረቱ ጣልቃ የመግባቱ አላማም ግራ አጋቢ ነዉ።አንድን ገዢን ማስወገድ? ከሆነ -ሳዳም ሁሴንን፥ ሙላሕ መሐመድን ዑመርን፥ቃዛፊን ከየአብያተ -መንግሥቱ አሸቀንጥሮ መጣል፥ መግደሉ በርግጥ ተችሏል።አሰድን መድገሙም አይገድም።ከዚያስ? ጆርጅ ቡሽ ይሉት እንደነበረዉ ሰላም እና ዲሞክራሲ ማስረፅ?-ያኒንግ «ሐሰት» ይሉታል።

«እኔ በግሌ እንደማምነዉ በሌለኛዉ የዓለም ክፍል በጦር ሐይል ጣልቃገብነት ሠላማዊ፥ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መመሥረት እና ምጣኔ ሐብታዊ ብልፅግናን ማምጣት ይቻላል ብሎ ማሰብ ሥሕተት ነዉ።አይቻልም»

የተቻለዉ ኢራቅ፥ አፍቃኒስታን፥ ሊቢያ የሚታየዉ ነዉ።ትርምስ።በጀርመን ምክር ቤት የአሜሪካ ጉዳይ ኮሚቴ አባልና የአረንጓዴዉ ፓርቲ ፖለቲከኛ ኦሚድ ኑሪፖር በበካላቸዉ አሜሪካ ሶሪያ ጦር የማታዘምተዉ በሁለት ምክንያት ነዉ ባይ ናቸዉ።አንደኛዉን ይጠይቃያሉ፥ «መርዛማዉን ጋዝ የተኮሰዉ ማነዉ?» ብለዉ።ሁለተኛዉ፥-

«በሐገሪቱ (ሶሪያ) ዉስጥ አደገኛ ጦርነት እየተደረገ ነዉ።የገንዘብ አቅማቸዉም ጣልቃ ለመግባት የሚያችል አይነት አደለም።ይሕ ማለት አሜሪካኖች ጦር ለማዝመት የሚያስፈልገዉ ነገር ሁሉ የላቸዉም።»

ATTENTION EDITORS - REUTERS CANNOT INDEPENDENTLY VERIFY THE CONTENT OF THE VIDEO, OBTAINED FROM A SOCIAL MEDIA WEBSITE, FROM WHICH THIS STILL IMAGE WAS TAKEN A still image taken from video posted on the Internet by opposition activists shows what they say is a ball of fire rising after an explosion in the central Syrian city of Homs on August 1, 2013. Forty people were killed and at least 120 people were wounded in an explosion at a weapons cache in the central Syrian city of Homs on Thursday (August 1), a group opposed to President Bashar al-Assad said. Amateur video posted on the Internet by opposition activists appeared to show a huge explosion in a neighbourhood inhabited mainly by Alawites - the same sect as Assad - blasting a fireball hundreds of metres into the air. REUTERS/Social Media Website via Reuters TV (SYRIA - Tags: CONFLICT TPX IMAGES OF THE DAY) NO SALES. NO ARCHIVES. FOR EDITORIAL USE ONLY. NOT FOR SALE FOR MARKETING OR ADVERTISING CAMPAIGNS. THIS IMAGE HAS BEEN SUPPLIED BY A THIRD PARTY. IT IS DISTRIBUTED, EXACTLY AS RECEIVED BY REUTERS, AS A SERVICE TO CLIENTS
ጦርነቱ-ሆምስምስል Reuters
Syria's President Bashar al-Assad delivers a speech while attending an Iftar, or breaking fast session, during the Muslim month of Ramadan in Damascus in this handout photograph distributed by Syria's national news agency SANA on August 4, 2013. Other attendees include political party representatives, politicians, independent figures, Muslim and Christian religious figures, representatives of unions and syndicates, and civil society figures. REUTERS/SANA/Handout via Reuters (SYRIA - Tags: POLITICS RELIGION) ATTENTION EDITORS - THIS IMAGE WAS PROVIDED BY A THIRD PARTY. FOR EDITORIAL USE ONLY. NOT FOR SALE FOR MARKETING OR ADVERTISING CAMPAIGNS. THIS PICTURE IS DISTRIBUTED EXACTLY AS RECEIVED BY REUTERS, AS A SERVICE TO CLIENTS FREI FÜR SOCIAL MEDIA
ምስል REUTERS/SANA

ሥለዚሕ አሜሪካኖች ቢያንስ ላሁኑ ጡንቻዉን ሰበብ ማድረጉን ነዉ-የመረጡት።

ነጋሽ መሐመድ

ተክሌ የኋላ