1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በለንደን የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አቀራራቢና ሽልማት ሰጪ ማኅበር፣

እሑድ፣ መጋቢት 27 2001

በአሁኑ ዘመን ፣ ኢትዮጵያውያን የማይገኙበት የዓለም ክፍል ያለ አይመስልም።

https://p.dw.com/p/HQkg
በሀገር ውስጥ የሚገኙ፣ ኢትዮጵያውያን ልጆች፣ምስል UNO

አውሮፓ ፣ አሜሪካ እስያም ሆን አውስትሬሊያ የሚገኙት የትውልድ አገራቸውን ባህል፣ ታሪክ ሥነ-ጽሑፍ ሙዚቃ---ልጆቻቸው እንዳይረሱ ለማስተማር፣ የማንነት መለያቸውንም እንዳያጡ፣ በሌላ በኩልም ከሚኖሩበት ሀገር ነባር ህዝብ ጋር ተስማምተው እንዲኖሩ ጥረት ያደርጋሉ። አውሮፓ ውስጥ፣ በብሪታንያ በተለይም በግዙፉ ከተማ በለንደን፣ የሚገኙት፣ በተለያዩ የሙያ መስኮች የሚያደርጉትን የሥራ እንቅሥቃሴና ግንኙነት በማበረታታት ላይ መሆኑን እንዳሥመሠከረ የተነገረለት የሀበሻ የንግድ ማኅበር የተሰኘው ድርጅት፣ በማኅበራዊ ኑሮ ግንኙነት በየዘርፉ እንዲጠናከር ለጣሩና አግልግሎት ላበረከቱ ከዚያም አልፎ በትውልድ ሀገር ውስጥ ፣ የጎዳና ተዳዳሪዎችንና እጓለ-ማውታንን ለሚረዱ «አርአያነት ያለው ተግባር ነው »በማለት ሽልማት ሰጥቷል። ስለሸላሚው ድርጅት ና ስለተሸላሚዎቹ፣ ከለንደን፣ ሐና ደምሴ ያጠናቀረችው ዝግጅት ቀጥሎ ይቀርባል።

ሐና ደምሴ፣

ተክሌ የኋላ፣

►◄