1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሊቢያ እና ስደተኞች ጉዳይ የመከረዉ የአዉሮጳ ኅብረት  

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 11 2009

የአውሮጳ ኅብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ትላንት በቤልጅየም ብራስልስ ስብሰባቸው በሊቢያ ፖለቲካ እና የስደተኞችን ጉዳይ ተወያይተው ውሳኔዎችን አሳልፈዋል። ሚኒስትሮቹ በሰ/ ኮሪያ ላይም ተወያይተው አካባቢውን ከኒዩክለር የጦር መሳሪያ ስጋት ለመታደግ ኅብረቱ ከዓ/አቀፉ ኅ/ሰብ ጋር በጋራ እንደሚሰራ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቀዋል፡፡

https://p.dw.com/p/2gkfE
Belgien EU-Flaggen auf Halbmast in Brüssel

European flags fly at half-mast to pay tribute to the victims of the terrorist attack in the Christmas Market in Berlin, Germany)
ምስል EU/J. Jacquemart

Ber. Brussels (EU Foreign Ministers meeting on Migration) - MP3-Stereo

በተጨማሪም ሚኒስትሮቹ የዘንድሮው ዓመት ከፍተኛ የምግብ እጥረት እና የደህንነት ስጋቶች የተጋረጡበት ዓመት መሆኑን በመጥቀስ በተለይም በሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሰሜን ናይጄሪያ እና የመን ከፍተኛ የረሃብ አደጋ የተከሰተ መሆኑን አስገንዝበው በእነዚህ ሀገራት ሊደርስ የሚችለውን እልቂት ለማስቀረት ህብረቱ እና አባል መንግስታት የሚያደርጉትን ጥረት ሌሎች ለጋሽ ሀገሮችም እንዲያግዟቸው ጥሪ አቀርበዋል፡፡

ገበያው ንጉሴ 

ተስፋለም ወልደየስ

አዜብ ታደሰ