1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሊባኖስ አመፅ መስፋፋቱ

ሰኞ፣ ጥቅምት 12 2005

በመኪና በተጠመደ ፈንጂ ከተገደሉት ከፍተኛ የደህንነት መስሪያ ቤት ባለስልጣን ዊሳም አል-ሃሳን የቀብር ስነ-ስርዓት በኋላ የሊባኖስ መዲና ቤሩት ግጭት ተስፋፍቶባታል። ትናንት ማምሻዉን ዛሬም እንዲሁ በተለያዩ አካባቢዎች ጥይት ጥቂት የማይባሉትን ዜጎች ህይወት አጥፍቷል።

https://p.dw.com/p/16Uhj
GettyImages 154523267 A Lebanese supporter of the March 14 movement, which opposes the Syrian regime of President Bashar al-Assad, demonstrates waving his national flag, as other protesters tried to storm the governmental palace, after the funeral of top intelligence chief General Wissam al-Hassan and his bodyguard, in downtown Beirut, on October 21, 2012. Lebanese police fired in the air and used tear gas to repel protesters trying to storm the office of Lebanese Prime Minister Najib Mikati, amid calls for him to quit. AFP PHOTO / JOSEPH EID (Photo credit should read JOSEPH EID/AFP/Getty Images)
ምስል AFP/Getty Images

ከቤሩት የሚወጡ አንዳንድ ዘገባዎች አመፅ ግጭቱ የሃይማኖት ፅንፍ እንዳይዝ ስጋታቸዉን ያመለክታሉ። በሌላ በኩል ሟቹ የሊባኖስ ከፍተኛ የደህንነት ባለስልጣን ከሶርያ መንግስት ተቀናናቃኞች ቅርበት እንደነበራቸዉ ተገልጿል። የሊባኖስ መንግስት ግድያዉ በሶርያ ካለዉ የዕርስ በርስ ጦርነት ጋር ተያያዥነት እንዳለዉ ይጠረጥራል።

ተቃዋሚዎች ሊባኖስ ውስጥ የሶሪያ መንግስት ደጋፊዎችን ለመቃወም ሰልፍ ጠርተው ነበር። ያኔ ነበር ብጥብጡ ተጀመረ። አርብ ዕለት በመኪና ላይ በተጠመደ ፈንጂም ዊሳም አል-ሃሳን እና ሌሎች ሰባት ሰዎች ተገደሉ። በዚሁ ፍንዳታ 80 የሚሆኑም ቆሰሉ። ቦንቡ የሶሪያ ፕሬዚዳንት ባሽር አሳድን መንግስት ከሚቃወመው ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት 200 ሜትር ርቀት ላይ ነዉ የፈነዳው። ለፍንዳታው እስካሁን ማንም ኃላፊነት አልወሰደም። የሊባኖስ አንዳንድ ባለስልጣናት በጥቃቱ የሶሪያ እጅ አለበት እያሉ ነዉ።

Members of the Internal Security Forces carry the coffin of slain intelligence officer Wissam al-Hassan as his family mourn during an official ceremony to pay tribute to Hassan at the Internal Security Force headquarters in Ashrafiyeh October 21, 2012. Thousands of people gathered in central Beirut on Sunday for the funeral of the assassinated senior intelligence officer, accusing Syria of involvement in the killing and calling for Lebanese Prime Minister Najib Mikati to quit. REUTERS/Mohamed Azakir (LEBANON- Tags: POLITICS CIVIL UNREST)
የዊሳም አል-ሃሳን የቀብር ስነ-ስርዓትምስል Reuters


በዊሳም አል-ሃሳን የቀብር ስነ-ስርዓት ላይ የተቆጡ ዜጎች ወደጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅህፈት ቤት ለመግባት እንቅስቃሴ ጀመሩ። ፀጥታ አስከባሪዎች ርምጃዉን ለመግታትና ህዝቡን ለመበተን አስለቃሽ ጭስ ሲረጩ፤ ህዝቡ በፋንታዉ ድንጋይ እና ብረት ወረወረ። በደህነት ባለስልጣኑ መገደል ሃዘንና ብስጭቱን የገለፀዉ ህዝብ ጠቅላይ ሚኒስትር ናጂብ ሚካቲ ስልጣን እንዲለቁም ጠይቋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሶሪያ መንግስት ጋ የጠበቀ ግንኙነት አላቸው ሲሉም ይወቅሳሉ።

A Lebanese protester throws back a tear gas canister at security forces, unseen, during clashes after the funeral of Brig. Gen. Wissam al-Hassan who was assassinated on Friday by a car bomb in Beirut, Lebanon, Sunday Oct. 21, 2012. Lebanese soldiers fired guns and tear gas to push back hundreds of protesters who broke through a police cordon and tried to storm the government headquarters in Beirut. The enraged crowd came from the funeral of a top Lebanese intelligence official assassinated in a massive car bombing.(Foto:Hussein Malla/AP/dapd)
የሊባኖሲያዊ ተቃዋሚ አስለቃሽ ጪስ ሲወረውርምስል AP


«በዊሳም አል-ሃሳን ሞት፣ ስለ ሀገራችን እና ስለ ራፊክ ሀሪሪ የተሰማንን ሀዘን እና ስቃይ መግለፅ እፈልጋለሁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ናጂብ ሚካቲ ሳይዘገዩ ዛሬውኑ ስልጣን እንዲለቁ እንጠይቃለን። ሚካቲ አሁኑኑ እንዲለቁ እናሳስባለን።» ይላሉ አደባባይ ከወጡት አንዱ። የሀሳን የቅርብ ወዳጅ የነበሩት የቀድሞዉ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ራፊክ ሀሪሪም እኢአ በ2005 ዓ ም ልክ እንደ በተመሳሳይ አደጋ መገደላቸዉ ይታወሳል። በእሳቸዉ ህልፈተ ህይወትም ጎረቤት ሀገር ሶሪያ ተጠርጣሪ ናት። የሀሪሪ ግድያም የሶሪያ እና የሊባኖስ ግንኙነትን እንዳበላቸዉ ይነገራል። በዚህ የተነሳም ሶሪያ በሊባኖስ ለአስርተ አመታት የነበራትን ጦር ከሀገሪቱ ማስወጣት ነበረባት። በስለላ ተግባር የተሰማራዉ አካል ግን አሁንም ሊባኖስ ዉስጥ እንደሚንቀሳቀስ ተገልጿል።

Lebanese policemen fire tear gas during clashes with angry protesters who attempted to storm the Lebanese government offices after the funeral of slain intelligence officer Wissam al-Hassan in Beirut October 21, 2012. Angry mourners marched on Lebanese Prime Minister Najib Mikati's offices in central Beirut on Sunday, breaking through an outer security barrier and scuffling with police who fired tear gas in response. REUTERS/Mahmoud Kheir (LEBANON - Tags: POLITICS CIVIL UNREST OBITUARY)
በሊባኖስ የተነሳው አመፅ እንደ ሶሪያ እንዳይስፋፋ ይሰጋልምስል Reuters


በሺ የሚቆጠሩ ሊባኖሳውያን ተቃውሞ የሚያሰሙባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ናጂብ ሚካቲ ስልጣን እንደሚለቁ አሳውቀው ነበር፤ ሆኖም የሀገሪቷ መሪ ይህንን ጥያቄ አላፀደቁትም። በዊሳም አል-ሃሳን የቀብር ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የሊባኖስ ፕሬዚዳንት ሚቼል ሱሌማን በበኩላቸዉ ወንጀለኞች ከለላ እንደማይሰጥ ነዉ በንግግራቸዉ ያመለከቱት፤
« ለፍትህ አካላት የማቀርበው ጥሪ ህዝቡ ከናንተ ጋ በመሆኑ እንዳትፈሩ ነው። የፀጥታ አስከባሪው ኃይልም የህዝቡ ድጋፍ ስላላችሁ በአቋማችሁ እንድትፀኑ ነው። ፖለቲከኞች፣ መንግስት እና የፖለቲካ ባለስልጣናት የወንጀል ርምጃዎችን እንዳትሸፋፍኑ ጥሪ አደርጋለሁ። ፖሊስ እና ዳኛ ደህንነቱ፤ ወንጀለኞች ደግሞ ከለላ እንደሌላቸዉ ይሰማቸዉ! ይህ የእኛ እና የፖለቲካ መሪዎች ኃላፊነት ነው።»
የጀርመን መንግስት የሊባኖስ መረጋጋት ወደ አስከፊ ሁኔታ እንዳያመራ ስጋቱን ገልጿል። የመንግስት ቃል አቀባይ እስቴፈን ሳይበርት ዛሬ በሰጡት መግለጫ መራሂተ መንግስት መርክል ሁኔታዉ እንዳሳሰባቸው እና የሀገሪቱ ባለስልጣናትም የተነሳው አመፅ እንደ ሶሪያ እንዳይስፋፋ ማሳሰባቸውን ተናግረዋል።

ልደት አበበ
ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ