1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሙስና ተጠርጣሪ ባለስልጣናት ፍርድ ቤት ቀረቡ

ማክሰኞ፣ ግንቦት 6 2005

በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ የመንግስት ባለስልጣናት ዛሬ፥ ግንቦት 5 ቀን 2005 ዓም ፍርድ ቤት መቅረባቸው ታወቀ። ፍርድ ቤቱ ለነገ ከሠዓት በኋላ ተጨማሪ ቀጠሮ መያዙም ተገልጿል። በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል የጉምሩክ ኃላፊዎች የመንግስት ባለስልጣናትና ባለሀብቶች ይገኑበታል

https://p.dw.com/p/18X79
አቶ ብርሀኑ አሰፋምስል DW/Y. Gegziabher

የፌዴራል የፀረ ሙስና እና ስነምግባር ኮሚሽን በሙስና ተጠርጥረዋል ብሎ በቁጥጥር ስር ያዋላቸው የጉምሩክ ኃላፊዎችና ባለሀብቶች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው የምርመራ ጊዜ ተጠየቀባቸው። የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር ባለቤትም ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ ትናንት የቤት ካርታዎችንና ሠነዶችን ሲያሸሹ ተገኙ በሚል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፌዴራል ፖሊስ ገልጾዋል። የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ቀጣዩን ዘገባ አጠናቅሯል።
 


ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር

ማንተጋፍቶት ስለሺ

አርያም ተክሌ