በሙስና የተጠረጠሩ ሰዎችን ማሰር መቀጠሉ
ሐሙስ፣ ግንቦት 15 2005ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግሥት በሙስና የተጠረጠሩ ተጨማሪ ሰዎችን በቄጥጥር ሥር መዋሉን ፣ በተያዙትና ጥቆማ በተደረገባቸው ሰዎች ላይም ምርመራው መቀጠሉን አስታወቀ ። የፌደራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የስነምግባር ትምሕርትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ አሰፋ እስካሁን በአጠቃላይ 51 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ለዶቼቬለ ተናግረዋል ። በሙስና ተጠርጥረው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ወደፊት እንደሚጨምርም አስታውቀዋል ። መንግሥት ከጥቂት ሳምንታት በፊት ስለ ጀመረው ስለዚሁ የማሰር ዘመቻ አቶ ብርሃኑ አሰፋን በስልክ አነጋግረናል ።
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ