1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በማሊ የቀጠለው ውዝግብ

ቅዳሜ፣ ነሐሴ 5 2004

በሰሜን ማሊ አንሶንጎ በተባለዉ አካባቢ ያይን ምስክሮች እንዳስታወቁት፡ ሙስሊም ፅንፈኞች አንድ ሞተር ባይስክል ሰርቆዋል ያሉትን ሰዉ እጅ ባለፈው ሐሙስ እአአ ነሀሴ 9 ፡ 2012 ዓም ቆርጠዋል።

https://p.dw.com/p/15nqK
TO GO WITH AFP STORY BY SERGE DANIEL - EXCLUSIVE IMAGES A picture taken on July 16, 2012 shows fighters of the Islamist group Movement for Oneness and Jihad in West Africa (MUJAO) sitting in the courtyard of the Islamist police station in Gao. A group of armed youths has arrived in Gao from Burkina Faso, joining hundreds of other young African recruits who have come to sign up with radical Islamists controlling the northern Mali town. The new batch of youths will join others from Senegal and Ivory Coast milling about in the scorching heat in the courtyard of a building the jihadists have made the headquarters of their Islamic-law-enforcing police. AFP PHOTO / ISSOUF SANOGO (Photo credit should read ISSOUF SANOGO/AFP/GettyImages)
ምስል Getty Images

ባካባቢው የሸሪዓ ሕግ ማወጃቸውን ያስታወቁት በምሕፃሩ ሙዣዎ የተባለው ለአንድነትና ጂሃድ ንቅናቄ ዓማፅያን ከሌኦች ቡድኖች ጋ ባንድነት ካለፈው ሚያዝያ ወዲህ ሰሜናዊውን ማሊ ተቆጣጥረዋል። ይህ ሁኔታ ያሳሰባቸው ጎረቤት ሀገሮች ባማኮ የሚገኘው የማሊ መንግሥት በሀገሩ የቀጠለውን ውዝግብ ባስቸኳይ እንዲያበቃ ግፊት ያሳረፉ ሲሆን፡ ይህችኑ ምዕራብ አፍሪቃዊት ሀገር የጎበኙት የጀርመን የኤኮኖሚ ልማት ትብብር ሚኒስትር ድርክ ኒብል አስቸኳይ መፍትሔ እንዲገኝ አሳስባለች። ይሁንና፡ በዚች ውዝግቡ በተካረረባትና መከፋፈል ባሰጋት ሀገር ውስጥ በቅርቡ ሰላም እንዴት ሊመለስ ይችላል ነው ጥያቄው።

ደቡባዊውን ማሊ የጎበኙት የጀርመን የኤኮኖሚ ልማት ትብብር ሚኒስትር ድርክ ኒብል በሰሜናዊ ማሊ የሚታየው ሰብዓዊ ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ሆኖ ነው ያገኙት። ይሁንና፡ ሚንስቴራቸው በዚሁ አካባቢ ለሚኖረው ሕዝብ እንደሚፈለገው አስቸኳዩን ርዳታ ማቅረብ እንደማይችል ገልጸዋል።

Entwicklungsminister Dirk Niebel (FDP, r) wird am Donnerstag (09.08.2012) in Bamako, Mali, vom malischen Übergangspräsidenten Dioncounda Traoré (M) begrüßt. Bei den Gesprächen in der Hauptstadt ging es um eine Lösung des Konflikts in dem westafrikanischen Krisenstaat. An diesem Freitag läuft ein Ultimatum ab, bis zu dem die malische Übergangsregierung konkrete Pläne und einen Fahrplan zur schnellen Bildung einer «Regierung der nationalen Einheit» vorlegen soll. Foto: Jörg Blank dpa
ምስል picture-alliance/dpa


« ያካባቢው ፀጥታ ሁኔታ ሲፈቅድ ብቻ በቀጥታ ሕዝቡን የሚጠቅም ርምጃ እንወስዳለን። ከዚችው ሀገር ጋ የልማት ትብብሩን የምንጀምረው ግን ሕገ መንግሥታዊው ሥርዓት እንደገና ሲሟላ ይሆናል። » እስከዚያ ድረስ ግን ጀርመን ለተቸገሩት የሰሜን ማሊ ነዋሪዎች ቢያንስ የምግብ ርዳታ እንደምታቀርብ አስታውቃለች።


በማሊ ሁኔታዎች እንዲስተካከሉ በዋነኝነት ጥረት የጀመረው የምዕራብ አፍሪቃ መንግሥታት የኤኮኖሚ ማህበረሰብ በምሕፃሩ ኤኮዋስ ነው። በመጀመሪያ ደረጃ የማሊ የሽግግር መንግሥት በሀገሩ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት እንዲያቋቁም ግፊት ያሳረፈ ሲሆን፡ በሁለተኛነት ደግሞ ሰሜናዊውን የሀገሪቱን ከፊል ከተቆጣጠሩትና በመላ ማሊ የሸሪዓን ሕግ የማስተዋወቅ ዓላማ ይዘው ከተነሱት ሙሥሊም ፅንፈኞችም ጋ እየተደራደረ ነው፤ በሦስተኛ ደረጃ ደግሞ በአንድ ዓለም አቀፍ አጥቂ ኃይል ጣልቃ ገብነት ሰሜናዊ ማሊን ከሙሥሊሞቹ ፅንፈኞች ለማስለቀቅ ርምጃ እንደሚወስድም ዝቶዋል።

--- DW-Grafik: Peter Steinmetz
ምስል DW


ይህ ጥረቱ እስካሁን ውጤት አላስገኘም። ኤኮዋስ ለማሊ የሽግግር መንግሥት ብሔራዊ አንድነት መንግሥት እንዲያቋቁም ሰጥቶት የነበረው የጊዜ ገደብ ባለፈው ሐምሌ ወር ካለፈ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ያስቀመጠለት ቀነ ቀጠሮ ማሊን በቅርቡ ሊያረጋጋ ይችል ይሆናል የተባለው መንግሥት ሳይቋቋም አልፎዋል።


የጀርመን የኤኮኖሚ ልማት ትብብር ሚኒስትር ድርክ ኒብል የብሔራዊው አንድነት መንግሥት በሚቀጥሉት ሁለት ሣምንታት እንደሚቋቋም ተስፋ አድርገዋል።
« አዲሱ የብሔራዊው አንድነት መንግሥት ባፋጣኝ መቋቋም ይኖርበታል። ከዚያ በኋላ ሀገሪቱን ሊያረጋጉ እና በተግባር ሊተረጎሙ የሚችሉ ግልፅ ዓላማዎችን የያዘ ዕቅድ ሊወጣ ይገባል። »


ለማሊ ቀውስ መፍትሔ አፈላላጊው የኤኮዋስ ዋነኛ ተደራዳሪ የቡርኪና ፋሶ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጂብሪል ባሶሌ ወደሰሜን ማሊ በመጓዝ ከተለያዩት የሙሥሊም ፅንፈኞች ቡድኖች፡ ከሙዦዋ ተጠሪዎች ጋ ጭምር ተገናኝተዋል። ዶይቸ ቬለ ያነጋገረው የማሊ ዜጋ የሆነው ጋዜጠኛው ድሪሳ ሳንጋሬ እንዳስረዳው ግን፡ ሌቦች የሚሉዋቸውን ግለሰቦች እጅ ከሚቆርጡ ፅንፈኞችና አክራሪ ሙሥሊሞች ጋ የተጀመረው ድርድር በሀገሪቱ ብዙ እያከራከረ ነው።


« ሁሉም አይደሉም ድርድሩን የሚደግፉት። ለምሳሌ ሙሥሊሞቹ ፅንፈኞች የተቆጣጠሩዋት የጎአ ከተማ ከንቲባ ይህን ዓይነቱን ድርድር ይቃወማሉ፤ ምክንያቱም እንደርሳቸው አባባል ሊታመን የሚችል ተደራዳሪ የለም። »


ያም ቢሆን ግን ኤኮዋስ በድርድሩ ለመቀጠል ነው የወሰነው፤ የሙሥሊሞቹ የረመዳን ፆም ከአሥር ቀናት ገደማ በኋላ ሲያበቃ ድርድሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። ኤኮዋስ እንዳስታወቀው፡ ከ 3000 ወታደሮች በላይ የሚሰለፍበት አንድ አጥቂ ቡድን በማሊ ጣልቃ ይግባ አይግባ ስለሚለው ሀሳብም የጦር ጠበብት ካለፈው ሐሙስ ወዲህ በባማኮ ምክክራቸውን ቀጥለዋል። ግን እስካሁን የተመድ በማሊ ይህ ዓይነቱ አጥቂ ቡድን እንዲሰማራ ፈቃድ አልሰጠም። የማሊ የሽግግር መንግሥትም ቢሆን በዚህ ሀሳብ አኳያ እስካሁን ቁጥብነትን ነው ያሳየው።

አርያም ተክሌ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ዘገባና ትንታኔ

ዘገባና ትንታኔ