1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሶሪያ ላይ የአሜሪካ ዛቻና ሩሲያ

ሰኞ፣ ጳጉሜን 4 2005

ነሃሴ ወር አጋማሽ ሶርያ መንግስት በመርዘኛ ጋዝ ተጠቅሞአል ለተባለበት ወንጀል፤ ምዕራባዉያን አሳድ ላይ የአየር ጥቃት ለማካሄድ እቅዳቸዉ ላይ በሁለት ወገን የተከፈሉ ይመስላል። ሶርያ መንግስት በበኩሉ የኬሚካዊ መሳርያ ጥቃትን እንዳልፈጸመ እየገለፀ ነዉ።

https://p.dw.com/p/19eFL
U.S. Secretary of State John Kerry speaks during a news conference with Britain's Foreign Minister William Hague at the Foreign and Commonwealth Office in London September 9, 2013. Kerry said on Monday Syrian President Bashar al-Assad could avoid a military strike by turning over all his chemical weapons within a week but immediately made clear he was sure that would never happen. REUTERS/Susan Walsh/Pool (BRITAIN - Tags: POLITICS)
የዩናይትድ ስቴትሱ የዉጭ ጉዳይ ሚንስትር ጆን ኬሪምስል Reuters

ያ ወዳጅ ሩስያም ዩኤስ አሜዪካ በሶርያ ላይ ጦርነት ከማንሳት ይልቅ ለሰላም ስምምነቱ ጥረት ብታደርግ ይሻላል ስትል ዛሪ አስታዉቃለች። የዩኤስ ኤዉ ዉጭ ጉዳይ ሚንስትር ጆን ኬሪ በበኩላቸዉ ሶርያ ያላትን የኬሚካል መሳርያ በሳምንት ግዜ ዉስጥ ካስረከበች የአየር ጥቃቱ እንደሚነሳ ተናግረዋል።
የሩስያዉ የዉጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ዩናይትድ ስቴትስ በሶርያ ላይ ጦር ከማንሳት ይልቅ የሰላም ድርድር ጥረት ብታደርግ ይሻላል በሚለዉ ሃሳብ ላይ ሀገራቸዉ ከሶርያ ጋር መስማማቷን ገልጸዋል። እንደ ሰርጌ ላቭሮቭ አሜሪካ በሶርያ ላይ ያቀደችዉ የአየር ጥቃት ሽብርተኛነት እንዲስፋፋ ምክንያት ይሆናል። በሌላ በኩል የሶርያዉ ፕሬዚዳንት ባሽር አልአሳድ የያዙትን የኬሚካዊ መሳርያ በአንድ ሳምንት ካስረከቡ ሶርያ ከተዛተባት የአየር ድብደባ ትድናለች ሲሉ የዩናይትድ ስቴትሱ የዉጭ ጉዳይ ሚንስትር ጆን ኬሪ ዛሪ ተናግረዋል። ኬሪ ሀገራቸዉ ሶርያ ላይ የአየር ጥቃት ለማድረግ የወሰነችዉ የሶርያዉ ፕሬዚዳንት ባሽር አልአሳድ ዳግም መርዘኛ ጋዝን ጥቅም ላይ እንዳያዉሉ ለማስቆም ነዉ ሲሉ ትናንት ፓሪስ ላይ መናገራቸዉ ይታወቃል። ኬሪ ዩናይትድ ስቴትስ በአሳድ መንግስት ላይ ላቀደችዉ የአየር ድብደባ ድጋፍ ለማሰባሰብ በፓሪስ በተደረገዉ የአረብ ሀገራት ማህበር ተወካዮች ስብሰባ ላይ እንደገለጹት፤ ሀገራቸዉ ከሌሎች ሃገራት በጋራ ስለ ሶርያ ጉዳይ መፍትሄ ለማግኘት በመጣር ላይ ናት።
« በሶርያ ጣልቃ ለመግባት ከአንደኛዉ ቡድን ለመወገን ወይም የሶርያዉን የእርስ በርስ ጦርነት የራስዋ ጉዳይ አድርጋ ለመረከብ አይደለም»
የዉጭ ጉዳይ ሚንስትር ጆን ኬሪ በሶርያ ላይ ወታደራዊ ጥቃት እንዲደረግ በሚለዉ አቋም ከአስር የማያንሱ የአሜሪካንን አቋም የሚከተሉ ደጋፊዎች እንዳላት ትናንት ፓሪስ ላይ መናገራቸዉ ይታወቃል። ዛሪ ለስድስት የቴሌዥን ጣንያ ቃለ ምልስ እንደሚሰጡ የተነገረዉ የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በሶርያ ላይ ይደረግ ያሉትን ወታደራዊ ቅጣት ለማካሄድ አሜሪካዉያን እና የኮንግረስ አባላትን ለማሳመን የተቻላቸዉን ሁሉ እንደሚያደርጉ ነዉ የገለፁት።
በሌላ በኩል የሶርያ ወዳጅ የሆነችዉ ሩስያ ዩናይትድ ስቴትስ በሶርያ ላይ ጥቃት እንዳትጥል እየታገለች ትገኛለች። የሶርያ ፕሬዚዳንት ባሽር አልአሳድ ጅምላ ጨራሽ መሳርያን እንዳልተጠቀሙ በተደጋጋሚ መግለፃቸዉ ይታወቃል። የሩስያዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭና የሶርያዉ አቻቸዉ አል ሞአላም፤ ዛሪ ሞስኮ ላይ ተገናኝተዉ የተመድ የኬሚካል መሳርያ መርማሪ ቡድን ሶርያ ዉስጥ ዳግም ተመልሶ እንዲያጣራ ግፊት በማድረግ ዩናይትድ ስቴትስ በሶርያ ላይ የሰነዘረችዉን እጇን እንዳታነሳ አስጠንቅቀዋል። የሩስያዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ ከጦርነቱ ይልቅ ለሰላም ዉይይት ለመድረስ ጥረት ማድረግ ይገባል ይላሉ፤
« የሶርያ ተቃዋሚ ወገን መሪዎች ባለፈዉ ዓመት ሰኔ 23 ጄኔቭ ስምምነት የተደረሰበትን የመፍትሄ ሃሳብ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ማድረግ ይቻል ዘንድ የሰላሙን ጉባዔ ያላንዳች ቅድመ ግዴታ የሚደግፉ ስለመሆናቸዉ ግልጽና የማያዳግም ፈቃደኝነታቸዉን ያረጋግጡ ዘንድ ከመጠየቅ አንቦዝንም»
አሜሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደነገገን ቀይ መስመር የሶርያ መንግስት መጣሱን የምትከሰዉ፤ ሶርያ ዉስጥ ነሃሴ ወር አጋማሽ የተቃዋሚ ደጋፊዎች በሚገኙባቸዉ ከደማስቆ ወጣ ባለ አካባቢ በተተኮሰ ጅምላ ጨራሽ መሳርያ 426 ህፃናትን ጨምሮ ከአንድ ሽህ በላይ ሰዎች መገደላቸዉን ተከትሎ መሆኑ ይታወቃል።

The USS Nimitz, a nuclear-powered aircraft carrier which is currently supplemented by biofuel, sails about 150 miles north of the island of Oahu during the RIMPAC Naval exercises off Hawaii in this file photo from July 18,2012. The Nimitz and four other ships in its strike group moved into the Red Sea early September 1, 2013, U.S. defense officials said, describing the move as "prudent planning" in case the ships are needed for military action against Syria. REUTERS/Hugh Gentry/Files (UNITED STATES - Tags: MILITARY ENERGY BUSINESS MARITIME ENVIRONMENT)
ምስል Reuters
Russia's Foreign Minister Sergei Lavrov (R, front) shows the way to his Syrian counterpart Walid Moualem (L) during a meeting in Moscow September 9, 2013. REUTERS/Sergei Karpukhin (RUSSIA - Tags: POLITICS)
የዉጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌ ላቭሮቭና የሶርያዉ አቻቸዉምስል Reuters

አሁን በደረሰን ዘገባ መሰረት ደግሞ ሩስያ፤ ሶርያ ያላትን የኬሚካል ጦር መሳርያ በዓለማቀፉ ማሕበረሰብ ቁጥጥር ስር በማድረግ ከዩናይትድ ስቴትስ የአየር ድብደባና ዉድመት እንድትድን ጠይቃለች። ይህን የገለፁት የሩስያዉ የዉጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ናቸዉ።

አዜብ ታደሰ
ተክሌ የኋላ