1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኢትዮጵያ የሚሞቱ ህጻናት ቁጥር መቀነስ

ዓርብ፣ መስከረም 10 2006

ኢትዮጵያ ዉስጥ አምስት ዓመት ሳይሞላቸዉ የሚሞቱት ሕጻናት ቁጥር ባለፈዉ 20 ዓመት በሁለት ሶስተኛ መቀነሱ ተነገረ። በኢትዮጵያ ዉስጥ በየዓመቱ ከሚወለዱት ከ 1000 ህፃናት መካከል 5 ዓመት ሳይሞላቸዉ የሚሞቱት ሕጻናት ቁጥር፤

https://p.dw.com/p/19lJs
ARCHIV - Ein Mutter in Sri Lanka legt die Hand auf die Stirn ihres zwei TAge alten Kindes in Galle, südlich Colombo. Jeden Tag sterben nach Berechnungen des Kinderhilfswerks UNICEF weltweit 1500 Frauen durch vermeidbare Komplikationen bei Schwangerschaft oder Geburt. Sei 1990 seien das insgesamt zehn Millionen Frauen gewesen. Am meisten gefährdet seien Schwangere in Südasien und in Afrika südlich der Sahara. Zudem überleben jedes Jahr vier Millionen Neugeborene die ersten 28 Tage nach der Geburt nicht. Um die sogenannten Millenniumsziele einer nachhaltigen Verringerung dieser Zahlen zu erreichen, müssten sie bis 2015 um mehr als 70 Prozent reduziert werden, teilte am Donnerstag das Kinderhilfswerk der Vereinten Nationen in Johannesburg (Südafrika) im Jahresbericht zur weltweiten Lage der Kinder mit. Die Millenniumsziele der UN sehen im Vergleich zu 1990 eine Verringerung der Kindersterblichkeit um zwei Drittel vor. EPA/DENNIS M. SABANGAN +++(c) dpa - Report+++
ምስል picture-alliance/dpa

ባሁኑ ወቅት 68 መሆኑን የተመድ የህጻናት መርጃ ድርጅት (UNICEF)አስታዉቋል። ከ 20 ዓመት በፊት ከ 5 ዓመት በታች በሆነ ዕድሜ ውስጥ የሚሞቱ ከ 1000 - 200 እንደነበርም ተመልክቶአል። በኢትዮጵያ የሟች ህጻናት ቁጥር መቀነሱን በተመለከተ፤ የዶቼ ቬለዋ ሳንታ ብሎመን ከተመ የህጻናት መርጃ ድርጅት ቃል አቀባይ ጋር ተነጋግራ የዘገበችዉን አዜብ ታደሰ እንዲህ ታቀርበዋለች፤
«በኢትዮጵያ ብቻ በዓመቱ የ200,000 ህጻናት ህይወት ተርፎአል፤ በጣም ትልቅ ቁጥር ነዉ»
በኢትዮጵያ ያለዉ የህክምና ሁኔታ የተሟላ የሚባል አይደለም። እንድያም ሆኖ በሀገሪቱ የታየዉ የጤና አጠባበቅ ጉዳይ አበረታች ያለዉ፤ የተመ የህጻናት መርጃ ድርጅት፤ ለዉጡን አብዮታዊ ብሎታል። ለዉጡ በተለይ በአንድ ጉዳይ ላይ ወሳኝ ነበር ይላሉ፤ በተመ የህጻናት መርጃ ድርጅት ቃል አቀባይ ሻንታ ቢሎመን፤
«በርግጥም መንግስት በሀገሪቱ ያለዉን መሰረታዊ የጤና ክትትል ላይ ገንዘብ አፍስሶአል። መዋለ ንዋይ የማፍሰሱ ዋጋ ደግሞ ህይወታቸውን የሚያጡ ህጻናት ቁጥር መቀነሱ ነዉ።»
የኢትዮጵያ መንግስት ትኩረቱን ያደረገዉ በአብዛኛዉ፤ በገጠሩ አካባቢ ላይ ነዉ። በጎአ 2003 ዓ,ም በሀገሪቱ ያሉትን፤ በተለይም በአካባቢ መሰረታዊ የጤና ጥበቃ ክትትልን ለማሻሻል ዉሳኔን ማሳለፉ ይታወሳል። በበርካታ የአፍሪቃ ሀገራት የህክምና ተጠቃሚዎች በአብዛኛዉ የከተማ ንዋሪዎች ብቻ በመሆቸናዉ ዉሳኔዉን ያልተለመደ አድርጎታል።
«የኢትዮጵያያ መንግስት 38,000 የጤና ጥበቃ ሰራተኞችን ረዘም ባለ ትምህርት ለአንድ ዓመት አሰልጥኖአል። ከዚህ በተጨማሪ የህክምና አገልግሎቱ በትክክለኛ እና ጥሩ ባለሞያዎች እንደሚካሄድ ክፍያ እንዲኖረዉም አድርጎአል»
በገጠሩ አካባቢ በየቀበሌዉ ዉጤቱ፤ የህክምና ሞያን የሚያዉቁ እና አንድ ሕጻን ለሞት የሚያበቃዉን በሽታ ምንነት በማወቅ ህክምና የሚሰጡ፤ ቢያንስ ሁለት የህክምና ባለሞያዎች እንዲኖሩ ሆንዋል። ህጻናቱ ከሚጠቁባቸዉ በሽታዎች መካከል ደግሞ የተቅማጥ፤ የሳንባ እና የወባ በሽታዎች ይገኙበታል። ከዚህ በተጨማሪ የህክምና ባለሞያዎቹ በአካባቢዉ ለሚኖረዉ ማህበረሰብ፤ በመኝታ ግዜ የወባ መከላከያ አጎበር እንዲያደርግ በየግዜዉ ትምህርት ይሰጣሉ። ሌሎች የአፍሪቃ ሀገራት በኢትዮጵያ የታየዉን አመርቂ ስራ በምሳሌነት በመዉሰድ በየሀገሮቻቸዉ ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት ላይ ይገኛሉ። ሊሎች የአፍሪቃ ሀገሮች በተለይ በገጠሩ አካባቢ በሚገኙ አካባቢዎቻቸዉ ላይ የጤና ሞያ ስልጠና መስጠት ጀምረዋል። እንድያም ሆኖ በጤና ጥበቃ ረገድ አህጉሪቱ ገና ብዙ መሥራት ይኖርበታል። እንደ ተ መ የህጻናት የአስቸኳይ ሁኔታ መርጃ ድርጅት ዘገባ በአፍሪቃ አህጉር ከአምስት ዓመት እድሜ በታች ያሉ ህጻናት፤ በየዓመቱ በቀላሉ በሚድን በሽታ ወደ አምስት ሚሊዮን ህጻናት ይቀጠፋሉ።

አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሃመድ

በኢትዮጵያ የሚሞቱ ህጻናት ቁጥር መቀነስ
ምስል DW
ARCHIV - Ein unterernährtes Kind wartet mit seiner Mutter im Krankenhaus von Dilla in Äthiopien auf Behandlung (Archivfoto vom 12.03.2003). Der Große Hunger in Äthiopien im Jahr 1984 sprengte selbst die Dimensionen von Elend und Katastrophen in Afrika, an die sich so viele Menschen im fernen Europa oder Nordamerika schon längst gewöhnt hatten. Rund eine Million Menschen starben Schätzungen zufolge im Hungerwinter 1984/1985. Als Ende Oktober 1984 die ersten Fernsehbilder um die Welt gingen, war es schon zu spät, war die Katastrophe nicht mehr aufzuhalten. Der Kreislauf von Dürre, Missernten und viel zu wenig Regen, unter dem Äthiopien, eines der ärmsten und am dichtesten bevölkerten Länder Afrikas immer wieder zu leiden hatte, mündete einmal mehr im Disaster. Foto: STEPHEN MORRISON (zu dpa-KORR "Vor 25 Jahren: Hungerkatastrophe in Äthiopien" vom 18.10.2009) +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture alliance/dpa
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ