1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኤች አይ ቪ ላይ አተኩረዉ የሚሰሩ ድርጅቶች ጥምረት

ሐሙስ፣ ሰኔ 16 2003

በሐዋሳ የሚንቀሳቀሱ ትኩረታቸዉን በኤች አይቪ ቫይረስ ላይ አድርገዉ የሚሠሩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጥምረት ፈጥረዉ መንቀሳቀስ መጀመራቸዉን አመለከቱ።

https://p.dw.com/p/RVQ7
ምስል AP

ከአንድ መቶ በላይ እንደሆኑ የተገለጸዉ እነዚህ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጥምረቱን የፈጠሩት በቫይረሱ ላይ የከፈቱትን ዘመቻ በጋራ አጠናክረዉ ለመቀጠል እንደሆነ ተገልጿል። ይህ አዲሱ ስልት የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት በተናጠል የሚደረገዉን ጥረት በአንድነት በማምጣት በተጠናከረ መርሃግብር አማካኝነት ዘመቻዉን ለማካሄድ እንደሚጠቅም ተመልክቷል። በዚህ ጥረትና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶችም የቫይረሱ ስርጭት የመቀነስ አዝማሚያ ማሳየቱ ነዉ የተገለጸዉ።

ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር

ሸዋዬ ለገሠ

አርያም ተክሌ