1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በእስራት ያሉት የበቀለ ገርባና የጓደኞቻቸው የረሃብ አድማ

Merga Yonas Bulaማክሰኞ፣ ሐምሌ 19 2008

በኦሮምያ ክልል በማስተር ፕላኑ ሰበብ የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ተከትሎ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ዋና ጸሐፊ፣ አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ 21 የፓርቲዉ ኮሚቴ አባላት በእስር ላይ ይገኛሉ።

https://p.dw.com/p/1JWDZ
Äthiopien Oppositionpartei MEDREK PK
ምስል DW/G. Tedla

[No title]

አቃቤ ሕግ 22ቱ ታሳሪዎች ላይ ክስ ሲመሰርት የአገሪቱን የፀረ-ሽብር ሕግ ተጠቅሞ ሲሆን፣ ተከሰሾቹ ግን ክሱን ውድቅ በማድረግ እየተከራከሩ መሆናቸውን ጠበቃቸው አቶ ኢብሳ ከተወነጀሉበት ክስ ነፃ መሆናቸዉ ከችሎት የሚወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ። ከዚያም አልፎ የእስረኞችን አያያዝ እና ወህኒ ቤት ዉስጥ የሚደርስባቸዉ የተለያዩ በደሎችን በተመለከተ አቶ በቀለ ገርባ እና ሌሎች የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ኮሚቴ እስረኞች፣ ችግራቸዉ እንዲሰማላቸዉ ታስረዉ ባሉበት ማረምያ ቤት ላለፉት ስድስት ቀናት የረኃብ አድማ ላይ መሆናቸዉን የገለፁት የፓርትዉ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ገብሩ ገብረማርያም ፤ ከረሃቡ አድማ በኋላ የሆነዉን ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል።

የእስረኞቹ ጠበቃ አቶ ወንድሙ ኢብሳ እስረኞቹ የረኃብ አድማ የመቱበትን ምክንያቶች የእስር ቤት ዉስጥ ያለዉን የኢስረኞች አያያዝ እንድሁም አሁን አገርቱ ዉስጥ ያለዉን ተቃዉሞ አስመልኪቶ መሆኑን ይናገራሉ።

የረሀብ አድማ የመቱት እስረኞች ላይ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ አንድ መፍትሔ ሊሰጥ ይገባል ስሉ ጠበቃ አቶ ወንድሙ ጠቅሰዋል።

ለበለጠ መረጃ አዉዲዮን ያዳምጡ

መርጋ ዮናስ

አረያም ተክሌ