1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኮብል ስቶን የመንገድ ስራ የተሰማሩ ወጣቶች

ዓርብ፣ መጋቢት 6 2005

የኮብል ስቶን የመንገድ ስራ ምን ያህል የትምህርት ብቃት ይጠይቃል? ስራውንስ እነማን ናቸው የሚሰሩት? ምክንያታቸውስ?

https://p.dw.com/p/17xWn
Keywords fussgänger fussgängerweg gemalt hinweis kind mutter pflasterung steine strasse symbol untergrund verkehr weg weiss zeichnung Land Deutschland URL http://de.fotolia.com/id/383694 Anne Katrin Figge - Fotolia.com
ምስል Fotolia/Anne Katrin Figge

በአንዳንድ የኢትዮጵያ ከተሞች « የኮብል እስቶን» መንገዶች ይታያሉ። በዚህ የተቀረፁ ድንጋዮችን በመደርደር የሚሰራው የመንገድ ስራ ላይ ደሳለኝ ተስፋዬ ፣ሃና ለማ እና ቢንያም ከድር ተሰማርተው ይሰራሉ። ደሳለኝ ትምህርቱን ከ10ኛ ክፍል፤ ሃና ደግሞ ከ8ኛ ነው ያቋረጡት። ቢንያም ከድር ደግሞ ሃና እና ደሳለኝን በመንገድ ስራ ቀጥሮ ያሰራል። እንዴት ለዚህ እንደበቃ ገልፆልናል።

ደሳለኝ ምንም እንኳን ጥሩ ውጤት ባይመጣለትም እስከ 10ኛ ክፍል ትምህርቱን ተከታትሏል። የኮብል እስቶን ስራ በአሁኑ ሰዓት የተማረውም ያልተማረው እየሰራው ይገኛል ይላል ወጣቱ። የወደፊት አላማው በትምህርቱ መቀጠል ነው። ሃና ደግሞ ሱቅ መክፈት ትፈልጋለች። ወጣቷ ወደዚህ የመንገድ ስራ ከመግባቷ በፊት በቤት ሰራተኝነትም ተቀጥራ ለሁለት አመት ሰርታለች። ሁለቱንም የስራ መስኮች ታነፃፅራለች።

የሁሉንም መልስ ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።

ልደት አበበ

ሒሩት መለሰ