1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ተቃዋሚ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች መታሰራቸው ፣ የአምንስቲ ተቃዉሞ

ሐሙስ፣ መስከረም 4 2004

የኢትዮጵያ ፖሊስ የሐገሪቱን ሠላምና ፀጥታ ለማደፍረስና ሕገ-መንግሥታዊዉን ሥርዓት ለማፍረስ አሲረዋል ያላቸዉን አራት የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትና አንድ ጋዜተኛን አሰሠረ።

https://p.dw.com/p/Rlt5

ፖሊስ እንደሚለዉ ተጠርጣሪዎቹ የታሠሩት በአሸባሪነት ከተፈረጁ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ሐገሪቱን ለማወክ መዶለታቸዉን የሚጠቁም መረጃ ሥለደረሰዉ ነዉ።ሰወስት አባባላቱ የታሠሩበት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ግን የፖሊስን መግለጫ አጣጥሎ ነቅፎታል።ፓርቲዉ እንዳስታወቀዉ አባላቱን ለማስፈታትና የሕዝብን ነፃናት እና መብት ለማስከበር የሚያደርገዉን ትግል ይቀጥላል።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ታደሰ እንግዳዉ ዝር ዝር ዘገባ ልኮልናል።የኢትዮጵያ መንግሥት እርምጃ የኢትዮጵያ መንግሥት የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትንና ጋዜጠኞችን በሸባሪነት ጥርጣሬ ማሰሩን አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምንስቲ ኢንተርናሽናል ተቃወመዉ።በድርጅቱ የኢትዮጵያና የኤርትራ ጉዳይ አጥኚ ክሌር በስተን ዛሬ እንዳሉት የኢትዮጵያ መንግሥት ሰዎችን በአሸባሪነት ስም የሚያስረዉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፥ የመብት ተቆርቋሪ ተቋማትንና ጋዜጠኞች የሚያስመቱትን ቅሬታና ተቃዉሞ ለማፈን ነዉ።የኢትዮጵያ መንግሥት የእስረኞቹን ሕጋዊ መብት እንዲያከብርም በስተን ጠይቀዋል።የለንደኑ ወኪላችን ድልነሳ ጌታነሕ ክሌር ቤስተንን አነጋግሮ የላከልን ዘገባ አለ።

ታደሰ እንግዳዉ

ድልነሳ ጌታነሕ

ነጋሽ መሐመድ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ