1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ቱርክ፣ የአውሮጳ ህብረት እና የሶርያ ስደተኞች

ማክሰኞ፣ መስከረም 25 2008

የቱርክ ፕሬዚደንት ሬቼፕ ጠይፕ ኤርዶኻን ትናንት በብራስልስ ባደረጉት ይፋ ጉብኝት ከአውሮጳ ህብረት ባለስልጣናት ጋር ተገናኝተው ወደ ህብረቱ አባል ሃገራት በብዛት ስለሚመጡት ስደተኞች ጉዳይ መከሩ።

https://p.dw.com/p/1GjW3
Brüssel Donald Tusk Treffen mit türkischem Präsidenten Tayyip Erdogan
ምስል Reuters/F. Lenoir

ህብረቱ በተለይ የሶርያን ስደተኞች መተላለፊያ ያደረጉዋት ቱርክ የስደተኞቹን ፍልሰት በማከላከሉ ረገድ እንድትተባበር ይፈልጋል። ወደ ሁለት ሚልዮን የሚጠጉ የሶርያ ስደተኞችን የምታስተናግደው ቱርክ በበኩሏ ከህብረቱ የፋይናንስ ድጋፍ፣ ለዜጎችዋ የቪዛ መላላትን የመሳሰሉ በርካታ ጥያቄዎች አቅርባለች። ስለ ቱርክ ፕሬዚደንት ኤርዶኻን እና ስለህብረቱ ባለስልጣናት ውይይት የብራስልሱ ወኪላችን ገበያው ንጉሤ ይህን ዘገባ ልኮልናል።

ገበያው ንጉሤ

አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ