1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ትኩረት በአፍሪቃ

ቅዳሜ፣ ነሐሴ 26 2004

ሞምባሳ ውስጥ የተገደሉት መንፈሳዊ መሪ፣አዲሱ የምክር ቤት አፈጉባኤ በሶማሊያ፣ምክር ቤታዊ እና ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በአንጎላ

https://p.dw.com/p/161mb
CORRECTS DATE TO AUG. 27, INSTEAD OF AUG. 2 - People carry the body of Aboud Rogo, a Muslim cleric who was facing terror-related charges, from the scene where he was shot dead near the Jomo Kenyatta public beach in Kenya's coastal city of Mombasa Monday, Aug. 27, 2012. The assassination of Rogo, a Muslim cleric accused by Washington and the United Nations of supporting al-Qaida-linked militants in Somalia, sparked rioting by youths who burned at least one police car and stoned businesses. Human rights groups say Rogo's murder falls into a pattern of extrajudicial killings and forced disappearances of suspected terrorists, allegedly being orchestrated by Kenyan police. (Foto:AP/dapd)
ምስል dapd

የኬንያ የወደብ ከተማ ሞምባሳ ሰሞኑን እረፍት ሳታገኝ ነው የሰነበተችው። አንድ መንፈሳዊ መሪ ሼክ አቦድ ሮጎ መሐመድ ሰኞ ዕለት በጥይት ተመተው ከተገደሉ በኋላ በሞምባሳ ከተማ ግጭት መነሳቱ ይታወሳል።

« አገሪቷን በጉልበተኛ ስርዓት አመራር ልናራምድ አንችልም  ሲሉ የኬንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ዕሮቡ ዕለት፤ የኬንያ ፕሬዚዳንት ሙአይ ኪባኪ እንዲሁ ዓመፁ ወደተካሄደበት ቦታ ተጉዘው ሀሙስ ዕለት መቻቻል በሞምባሳ ከተማ እንዲወርድ ጥሪ አድርገዋል።

« በፍፁም መጥፎ ተግባር የሚፈፁሙ ኃይላት እንዲከፋፍሉን በምንም መንገድ መፍቀድ የለብንም። የአገሪቷን የሰላም መድረክ እና የብሔራዊ ሰላም ጉባኤዎችን ማጠናቀቃችን ነው። በነዚህ ዝግጅቶች ወቅት ኬንያውያን አንዳቸው ከሌላኞቻቸው ጋ ተቻችለው የመኖርን አስፈላጊነት አጥብቀው ለመከተል በአንድነት ተስማምተዋል።»

Kenyan security forces patrol the streets during demonstrations following the shooting and killing of Aboud Rogo Mohammed, in Kenya's coastal city of Mombasa, August 27, 2012. Hundreds of protesters smashed cars and vandalised at least four churches in the Kenyan city of Mombasa on Monday after unknown gunmen shot dead Aboud Rogo Mohammed, a Muslim cleric accused by the United States of helping Islamist militants in neighbouring Somalia. REUTERS/Joseph Okanga (KENYA - Tags: RELIGION CIVIL UNREST CRIME LAW TPX IMAGES OF THE DAY)
ለሁለት ቀናት በተካሄደው አመፅ ዓብያተ ክርስትያን እና መኪናዎች በእሳት ተለኩሰዋልምስል Reuters

ኪባኪ አክለውም ለችግሩ በፍጥነት መፍትሄ ማግኘት አለብን ነው ያሉት። ሼክ አቦድ ሮጎ መሐመድ ባልታወቀ ሰው ከተገደሉ በኋላ ደጋፊዎቻቸው ለሁለት ቀናት ባስነሱት አመፅ ዓብያተ ክርስትያን እና መኪናዎች በእሳት ተለኩሰዋል። በሱቆች ላይ ዘረፋ ተካሂዷል።  ዶቸቬለ ያነጋገራቸዉ በሞምባሳ የስነ ልቦና ቢሮ ተጠሪ አብዱልራህማን ባዳዊ ዉጥረቱ በሙስሊምና በክርስትያን መካከል አይደለም ይላሉ፤

«ጦርነቱ በክርስትያን እና በሙስሊም መካከል አይመስለኝም። እንዲህ አይነትነገር የለም። አመጹን ያስነሱት ሰዎች መሪያቸዉ ጥበቃ ስላልተደረገላቸዉ ነዉ የተበሳጩት። አንድ ግዜ ሟቹ፤ ህይወቴ አደጋ ላይ ናት ሲሉ ለጸጥታአስከባሪዎች ስሞታ አቅርበዉ ነበር ግን  ከዝያ በኋላም ምንም አይነት ጥበቃ አልተደረገም።በዝያ ላይ ደግሞ ሼክ ናቸዉ። ተከታዮቹ በሙሉ በጣም የተበሳጩት። ከተገደሉ በኋላተከታዮቻቸው ተቃዉሞአቸዉን በማሰማት ሱቆችን ተሽከረካሪዎችን አወድመዋል።ቤተ-ክርስትያን ላይ ሳይቀር ጥቃት አድርሰዋል።ግን ይሄ በክርስትያን እና በሙስሊም መካከል የተነሳ ጦርነት አይደለም።እንዲህም አይነት ነገር በኬንያም ሆነ በሞባሳ ከተማ ይከሠታል ብዬ አላስብም»  

FILE - In this photo of March 15 2000, controversial Muslim cleric Aboud Rogo is seen in in Nairobi High Court, Kenya, during his hearing on terrorism charges. Rogo has been shot dead at a beach in Mombasa according to local sources Monday Aug. 27 2012. Rogo was among three Kenyans whose assets were frozen by the US government over alleged links to terrorism. But the three Aboud Rogo, Abubaker Shariff Ahmed and Omar Awadh Omar denied the charges and challenged the US government to table evidence against them. The cleric was shot inside his car in front of his wife and children. Reports indicate that the wife was injured during the shooting and his 5 year old daughter was shot on her right leg.(Foto:Khalil Senosi, File/AP/dapd)
መንፈሳዊ መሪ ሼክ አቦድ ሮጎ መሐመድምስል dapd

ከቤተሰባቸው ጋ ከሞምባሳ ወደ ማሊንዲ ሲጓዙ በጥይት ህይወታቸው ያለፈው መንፈሳዊ መሪ፤ ከአሸባብ ቡድን ጋ ግንኙነት አላቸው ተብሎ ይታመናል። ለቡድኑም ሶማሊያ ውስጥ ገንዘብ እና ተዋጊዎች አቅርበዋል በማለት ይተቻሉ።ዩናይትድ እስቴትስ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአሸባሪነት እቀባ ከተደረገባቸው ስም ዝርዝር ውስጥ ከተዋቸዋል።

ናይሮቢ ውስጥ እኢአ 1998 ዓም በአሜሪካ ኤምባሲ ላይ ለደረሰው ጥቃት እና ከ200 በላይ ህይወት ለጠፋት አደጋ ዩናይትድ እስቴትስ ፤ ሼክ አቦድ ሮጎ ተጠያቂ ናቸው ብላ ደምድማለች።  የመንፈሳዊ መሪው በኬንያ ያለፍቃድ የጦር መሳሪያ በመያዝ ተከሰው ዋስ ከከፈሉ በኋላ ነው  የተለቀቁት።  በርግጥ ከግድያው በስተጀርባ ስላለው ሰው እስካሁን የኬንያ መንግስትም ይሁን የሰብዓዊ መብት ተሟጋጅ ድርጅቶች አልደረሱበትም። ርግጥ ግን በነበረው አመፅ እስከ ትናንት ረፋዱ ድረስ የ4 የፖሊስ አባላት እና 3 ሲቪሎች ህይወት አልፏል።  አመፁን ያካሄዱት ወጣቶች ከጎረኔት ሀገር ሶማሊያ ጋ ግንኙነት ያላቸው ሊሆኑ እንደሚችሉ የሞምባሳ ፖሊስ ምክትል ሃላፊ ሮበርት ኪቱር ለዶይቸ ቬለ ገልፀዋል።

« አገራችን ሙሉ በሙሉ ሰላም ነው። እነዚህ ጥቂት ወጣ ያሉ፤ ላለፉት ጥቂት ቀናት ሞምባሳ ውስጥ የተዘገቡ ጉዳዮች ናቸው። ግን ለህዝቡ ልገልፅለት የምወደው ማንኛውንም ህዝቡን ለማስፈራራት የሚጥር ታጣቂን ለመጋፈጥ ዝግጁ እንደሆንን ነው።»

Somali President Sheikh Sharif Sheikh Ahmed arrives to mark the first year anniversary since the ouster of militant Al Shabaab fighters from the capital Mogadishu August 6, 2012. REUTERS/Omar Faruk (SOMALIA - Tags: CIVIL UNREST POLITICS ANNIVERSARY)
ሼክ ሸሪፍ አህመድምስል Reuters

ያለፈው ማክሰኞ የሶማሊያ ምክር ቤት የቀድሞዉን ሚኒስትር ሞሀመድ ኦስማን ጃዋሪን አዲሱ የምክር ቤት አፈጉባኤ እንዲሁኑ ሾሞአል። ከተወዳደሩት 5 እጩዎች፤ ጃዋሪ መበጀመሪያው ዙር 119 ድምፅ በማምጣት የ2ተኛነትን ቦታ ከያዙት አሊ ክሊፍ ጋላር ፊት ተሰልፈዋል።  የጃዋሪ ማሸነፍ እንደተነገረ ጋላር  ወዲያውኑም ከእጩ ተወዳዳሪነት ራሳቸውን አግለዋል። ጃዋሪ ከደቡቡ የሶማሊያ ክፍል ባይዶዋ  ሲሆኑ ጎሳቸው ከአገሪቱ 4ተኛው ትልቅ የራሃንወይን ጎሳ ነው። ። አዲሱየሶማሊያየምክር ቤት አፈጉባኤ መምረጡ በርግጥ የተረጋጋ አመራር ላለፉት 20 ዓመታት ላልታየባት ሶማሊያ፤ አንድ ርምጃ ነው። ሆኖም  ጃሚር ለምክር ቤቱ አዲስ ሰው አይደሉም። በአምባ ገነኑ የሳይድ ባሬ ጊዜም ሚንስትር ነበሩ። በርግጥ ጃዋሪ ለሶማሊያ አዲስ ተስፋ ስለመሆናቸው በቀጣይነት የሚታይ ይሆናል።

የሀገሪቷ ባለስልጣናት፣እና የተባበሩት መንግስታት ተወካዮች አዲሱን አፈጉባኤ ሲያወድሱ የተባበሩት መንግስትታት ልዩ ተወካይ አውጉስቲን ማሂጃ ደግሞ ርብ ዕለት ምርጫው በሚቀጥሉት 10 ቀናት ውስጥ መካሄድ አለበት ብለዋል። የሶማሊያ ፕሬዚዳንታዊ የምርጫ ኮሚቴ ትናንት ከሰዓት እንዳስታወቀው ደግሞ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫው እኢአ መስከረም 10 ይካሄዳል።

Dere somalische Präsident Mohammed Siad Barre während der Islamischen Weltkonferenz im Januar 1981 in Riad (Saudi-Arabien).
ሞሐመድ ሳይድ ባሬምስል picture-alliance/dpa

የምክር ቤቱ አባላት ማክሰኞ ዕለት አዲሱን የምክር ቤት አፈጉባኤ ለመምረጥ እንደታሰበው በሶማሊያ ምክር ቤት ሳይሆን የተገናኙት ለደህንነት ሲባል፤ በአንድ የፖሊስ ትምህርት ቤት ነበር። ሆኖም ጉባኤው ጨርሶ በሞቃድሾ መካሄዱ ለበርካታ የምክር ቤቱ አባላት ትልቅ አንድ ርምጃ ነበር። እስካሁን እንደዚህ አይነት ስብሰባዎች ከሶማሊያ ውጪ ነበር የተካሄዱት። የሶማሊያን ህገ መንግስት ያፀደቁት 135 የሀገር ሽማግሌዎች እስከ ትናንት ድረስ ከሚፈለጉት 275 አባላት 260ውን አባላት መርጠዋል። የም/ቤቱ አባላት ቁጥር ከተሟላም በኋላ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ምርጫ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

አሁንም በስልጣን ላይ የሚገኙት ሼክ ሸሪፍ አህመድ ፕሬዚዳንት ሆነው በድጋሚ ለመመረጥ ከፍተኛ ዕድል አላቸው።

Bürger aus Luanda am Morgen des 31.08 stehen in Luanda an, um ihre Stimme abzugeben. Angola hält die 3. Wahlen in einem Mehrparteiensystem ab seit der Unabhängigkeit 1975. Der erste Kandidat der Liste von der Partei, die am meisten gewählt wird, wird automatisch zum neuen Präsidenten Angolas. Copyright: DW/António Cascais 31.08.2012
ምክር ቤታዊ እና ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በሉአንዳምስል DW

በምዕራብ አፍሪቃውቷ ሀገር አንጎላ ትናንት ምክር ቤታዊ እና ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ሲካሄድ ውሏል። 9 ሚሊዮን የሚደርስ ህዝብም ድምፁን እንዲሰጥ ጥሪ ተደርጓል። ገና ምርጫው ሳይካሄድ የ70 አመቱ ዶሴ ኤዱዓርዶ ዶስ ሳንቶስ አሸናፊ እንደሚሆኑ ሲገለፅ ሰንብቷል። ዶስ ሳንቶስ የአንጎላ ነፃ አውጪ ንቅናቄ ፓርቲ በምህፃሩ MPLA  መግዛት ከጀመረበት 33 ዓመት ጀምሮ በስልጣን ላይ ይገኛሉ።  ባካሄዱት የዘንድሮው የምርቻም ዘመቻ ሙሉ በሙሉ በራስ መተማመን አሳይተዋል።

« የሀገራችን መልሶ ግንባታ ተጠናክሯል። ስለሆነም የአንጎላውያን የህይወት ደረጃ እንዲሻሻል የበኩላችንን እያደረግን ነው። ከኔጋ ወደፊት መራመድ ይቻላል። ተቃዋሚዎች ግን ወቀሳ እና ዛቻ ነው የሚችሉት። እኛ MPLAዎች ግን ለአገራችን ልማት ነው የምንሰራው።»

አንጎላ ከፖርቹጋል ነፃ ከወጣች እኢአ 1975 ጀምሮ ነፃ ምርጫ ሲካሄድ በሀገሪቱ ገና 3ኛ ጊዜ ነው። ዶስ ሳንቶስ ድምፅ ለመስጠት ትናንት በመዲናይቱ ሉዋንዳ በተገኙበት ወቅትም « ይህ ኃላፊነት የምናሳይበት እና ሁሉም ድምፅ ሰጪዎች ያለባቸውን ህዝባዊ ግዴታ የሚወጡበት ጊዜ ነው ብዬ አስባለው ነው ያሉት።  

ጋሉፕ የተባለው የአሜሪካ ታዋቂ ተቋም ያለፈው አመት እንዳወጣው ጥናት ከሆነ ዶስ ሳንቶስ ከአፍሪቃ ተወዳጅነት ከሌላቸው መሪዎች አንዱ ናቸው። 16 ከመቶ የሚሆነው የአንጎላ ህዝብ ብቻ ነው እሳቸውን የሚያወድስ። የዝምባዊው ሮበርት ሙጋቤ እንኳን 30 ከመቶ በሚሆነው ህዝባቸው ዘንድ ተወዳጅነት እንዳላቸው ጥናቱ ያሳያል።

ይሁንና የ MPLAን ፓርቲ ስልጣን ላይ ከመቆየት የሚያዳግተው ያለ አይመስልም። ለዚህም ምክንያቱ የተጠናከረ የተቃዋሚ ፓርቲ ባለመኖሩ ነው። ለዘንድሮው ምርጫም ገዢው ፓርቲ  በምርጫ ዘመቻው ላይ ተፅዕኖ እንዳደረገ ፤ አንጎላዊው ጋዜጠኛ እና የሰብዓዊ መብት ተማጋች ራፌል ማርኮስ ከምርጫው በፊት ገልጿል።

A ballot paper is seen ahead of the national elections in the capital Luanda, August 31, 2012. "Victory is certain" runs the old war slogan of Angola's ruling MPLA party, and few doubt that a one-sided election on Friday will keep President Jose Eduardo dos Santos at the helm of Africa's second largest oil producer. Despite palpable discontent among ordinary Angolans about the unequal distribution of their country's oil wealth, Dos Santos' MPLA is expected to win most of the votes at the expense of much smaller and weaker opponents, including the former rebel group UNITA. REUTERS/Siphiwe Sibeko (ANGOLA - Tags: POLITICS ELECTIONS)
የምርጫ ወረቀትምስል Reuters

« አንጎላ ውስጥ ያለው የምርጫ ሂደት ገዢውን ፓርቲ በስልጣን ላይ እንዲቆይ የሚያደርግ ነው። ከፍተኛ ሙስና ያለበት ነው። ከ 9 ሚሊዮን ህዝብ 6,5 ሚሊዮኑ ድምፅን እንዴት እንደሚሰጥ አያውቅም። 1,5 ሚሊዮን የመራጭ ካርዱ በየምርጫ ጣቢያው መሳቢያ ተደብቀው ይገኛሉ።  ማንኛውም ጤናማ አስተሳሰብ ያለው አንጎላዊ ይህ ምርጫ በሰላም እና በሀቅ ይካሄዳል ብሎ አያምንም።»

 ከአንጎላ ሁለተኛው ትልቁ ፓርቲ ኃላፊ ኢሲያስ ሳማኩቫም ተመሳሳይ አስተያየት ነው በምርጫው ቀን የተናገሩት።  የመላው አንጎላ ብሔራዊ ነፃ አውጪ ህብረት መሪ እንዳስታወቁት ምርጫውን ተቀባይነት እንደማይሰጡት እና ለነፃ ምርጫው ወሳኝ የሆኑት ነገሮች ባለመሟላታቸው ፓርቲው አስቀድሞ  ምርጫው እንዲካሄድ  ማለቱን አሳስበዋል።

ከምርጫው ጥቂት ቀናት በፊት ለምርጫው ወሳኝ የሆኑ ነገሮች አለመሟላታቸውን ሊዛ ሪምሊ ተናግረዋል። ለሰብዓዊ መብት የሚሟገተው ድርጅት በሂውማን ራይትስ ዎች የአንጎላ ተንታኝ ናቸው።

Angola's President Jose Eduardo dos Santos (C) addresses the media after casting his vote during national elections in the capital Luanda, August 31, 2012. Angolans voted on Friday in a one-sided election expected to keep Eduardo dos Santos at the helm of Africa's No. 2 oil producer, but the long-serving leader faces swelling popular pressure to share the nation's riches more evenly. REUTERS/Siphiwe Sibeko (ANGOLA - Tags: POLITICS ELECTIONS MEDIA)
ዶስ ሳንቶስ « ይህ ኃላፊነት የምናሳይበት እና ሁሉም ድምፅ ሰጪዎች ያለባቸውን ህዝባዊ ግዴታ የሚወጡበት ጊዜ ነው ብዬ አስባለው ነው ያሉት።ምስል Reuters

« በ2008 ዓ ም በርካታ የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ነበሩ።  በሁሉም የአገሪቱ ክፍል ለረዥም ጊዜ ተመድበው ቆይተዋል። ባሁኑ ምርጫ ግን ቁጥራቸው ትንሽ የሆነ የምርጫ ታዛቢዎች ነው ያሉት። እስከዛሬ ድረስ ኤምባሲውን ጨምሮ ፍቃድ አልሰጧቸውም። ይህ የተለያዩ የሲቪሉን ድርጅቶችንም ይጨምራል። ከነዚህ መካከል በርካታ ገለልተኛነታቸው የታወቁ የሰብዓዊ መብት ተማጋች ድርጅቶች ይገኙበታል።»

ምንም እንኳን ተቃዋሚ ፓርቲዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ተቃውሞ ያሰሙ ቢሆንም ምርጫው ትናንት ተካሂዷል። እንደተገመተው የMPLA ፓርቲ ምርጫውን ካሸነፈ በቀጥታ የፓርቲው መሪ የፕሬዚዳንትነቱን ቦታ ይይዛሉ። ያም ሰው፤ ዶስ ሳንቶስ መሆናቸው ነው።

ልደት አበበ

መስፍን መኮንን