አልበሽር በአስመራ
ሰኞ፣ መጋቢት 14 2001ማስታወቂያ
የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው አልበሽር አሰመራ የገቡት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ባደረጉላቸው ግብዣ መሰረት ሲሆን ኤርትራ የሚቆዩትም ለአንድ ቀን ነው ። የኤርትራው ፕሬዝዳንት አጋርነታቸው በመግለፅ የሱዳኑ መሪ ኤርትራን እንዲጎበኙ የጋበዙዋቸው ዓለም ዓቀፉ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት በአልበሽር ላይ የዕስር ማዘዣ በቆረጠ በሳምንቱ ነበር ። አልበሽር አስመራ የገቡት በአረብሊግ ስብሰባ ላይ ለመካፈል ወደ ዶሀ እንዳይሄዱ የሀገሪቱ ከፍተኛ የሀይማኖት መሪዎች በጠየቁ ማግስቱ መሆኑ ነው ። የአስመራው ወኪላች ጎይቶም ቢሆን ዘገባ አለው