1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አሜሪካ የአርባ ምንጭ ሰው አልባ አውሮፕላን ተልዕኮን ዘጋች

እሑድ፣ ታኅሣሥ 24 2008

ዩናይትድ ስቴትስ አርባ ምንጭ፤ ኢትዮጵያ ይገኝ የነበረው የሰው አልባ አውሮፕላን ተልዕኮዋን መዝጋቷን አንድ የኤምባሲ ባለሥልጣን አስታወቁ። የዩናይትድ ስቴትስ ወታደራዊ ሠራተኞች ከእንግዲህ አርባ ምንጭ እንደማይኖሩ ዩናይትድ ስቴትስ አስታውቃለች።

https://p.dw.com/p/1HXRC
MQ-9 Reaper Drohne Drohnenkrieg Ziel Drohnenangriff Afghanistan
ምስል picture-alliance/AP/Air Force/L. Pratt

ኢትዮጵያ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ቃል-አቀባይ ዴቪድ ኬኔዲ የአርባ ምንጩ ሰው አልባ አውሮፕላን ማዕከል ከአሁን በኋላ አስፈላጊ አይደለም ሲሉ በኢሜል መልእክት መግለፃቸቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል። «የዩናይትድ ስቴትስ ወታደራዊ ሠራተኞች ከእንግዲህ በአርባ ምንጭ የሉም» ሲሉም ቃል አቀባዩ አክለዋል። ዩናይትድ ስቴትስ የሶማሊያው ጽንፈኛ ታጣቂ ቡድን አልሸባብ ላይ ቅኝት እና ጥቃት ለመሰንዘር ትጠቀምበታለች የተባለው የአርባ ምንጭ ማዕከል ስለመኖሩ በይፋ አረጋግጣ አታውቅም። ኢትዮጵያ የአልሸባብ ታጣቂ ቡድንን ለመዋጋት ወታደሮቿን ወደ ሶማሊያ ማዝመቷ አይዘነጋም። ምንም እንኳን የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ኢትዮጵያን በሰብአዊ መብቶች ጥሰት በተደጋጋሚ ሲወቅሱ ቢሰማም፤ ኢትዮጵያ ዩናይትድ ስቴትስ በምሥራቅ አፍሪቃ በምታካሂደው ፀረ-ሽብር ዘመቻ ዋነኛ ተባባሪ ናት።

እሸቴ በቀለ

ማንተጋፍቶት ስለሺ