1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አስደንጋጩ የላይቤሪያ ተማሪዎች ውጤት

ሐሙስ፣ ነሐሴ 23 2005

በአዲሱ የትምሕርት ዘመን ላይቤሪያ ዩኒቨርስቲ ያመለከቱ 25 ሺህ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተናውን መውደቃቸው የላይቤሪያ የትምህርት ደረጃ ዝቅተኛ መሆኑን እንደሚያመለክት የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ ሳይቀሩ አምነዋል ።

https://p.dw.com/p/19YkX
ምስል picture-alliance/dpa

ለላይቤሪያ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች በሙሉ መውደቃቸው ላይቤሪያውያንን ብቻ ሳይሆን በዓለም ዙሪያ እያነጋገረ ነው ። በአዲሱ የትምሕርት ዘመን ላይቤሪያ ዩኒቨርስቲ ያመለከቱ 25 ሺህ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተናውን መውደቃቸው የላይቤሪያ የትምህርት ደረጃ ዝቅተኛ መሆኑን እንደሚያመለክት የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ ሳይቀሩ አምነዋል ። ፕሬዝዳንቷ የተማሪዎቹ የፈተና ውጤት ለላይቤሪያ አሳፋሪ መሆኑንም ሳይጠቅሱ አላለፉም ዩኒቨርስቲው ወደ ተቋሙ መግባት የሚያስችለውን ነጥብ ዝቅ በማድረግ 1600 ፈተና ማለፍ ያልቻሉ ተማሪዎችን ለመቀበል ተገዷል ። ዝርዝሩን ይልማ ኃይለ ሚካኤል አዘጋጅቶታል ።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ