1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አተት በትግራይ እና በአማራ

ረቡዕ፣ ነሐሴ 11 2008

በትግራይ በአተት መንስኤ የሞተ አለ እየተባለ ቢነገርም የክልሉ የጤና ቢሮ ግን ይህን አስተባብሏል ።

https://p.dw.com/p/1Jjsg
EHEC-Bakterien Dossierbild 1
ምስል picture-alliance/dpa

[No title]

በትግራይ እና በአማራ ክልሎች አጣዳፊ ተቅማጥ እና ተውከት በምህፃሩ አተት በሰዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን የጤና ባለሞያዎች አስታወቁ ።የመቀሌ ሆስፒታል በበሽታው ለተያዙ የተለየ ቦታ ከልሎ የህክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆኑን ገልጿል ።ከዚሁ ጋር ሆስፒታሉ ስለ በሽታው ምንነት ስለ ሚተላለፍባቸው መንገዶች እና ስለ መከላከያው የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምሕርት በመስጠትም ላይ መሆኑን አስታውቋል ። በትግራይ በአተት መንስኤ የሞተ አለ እየተባለ ቢነገርም የክልሉ የጤና ቢሮ ግን ይህን አስተባብሏል ። አተት ከመቀሌ ሌላ በተለያዩ የአማራ ክልል አካባቢዎች መከሰቱም ተነግሯል ።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ኂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ