1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አንድነትና ብርሃን ፓርቲ መዋሃዳቸው

ሰኞ፣ ታኅሣሥ 2 2004

የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ከብርሃን ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ጋር ተዋሀደ ።

https://p.dw.com/p/S1gd
ምስል picture alliance/dpa

የሁለቱ ፓርቲዎች ውህድ የሆነውን አዲሱን አንድነት ለፍትህ እና ለዲምራሲ ፓርቲ እንዲመሩም ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳን በሊቀ መንበርነት መርጧል ። ፓርቲውን በበላይነት የሚመሩ 55 የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት ምርጫም አካሂዷል ። ጠቅላላ ጉባኤው ከዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያ ራድዪ ና ቴሌቭዥን አኬልዳማ በሚል ርዕስ ለህዝብ የሚቀርበው ፕሮግራም ፓርቲውን ከህዝብ ለመነጠል የታቀደ ነው ሲል ቅሬታውን ገልፃል ።

ታደሰ እንግዳው

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ