1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አወዛጋቢው የአልሲሲ የጀርመን ጉብኝት

ሐሙስ፣ ግንቦት 27 2007

የጀርመን ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ኖርቤርት ላሜርት ግብፅ ውስጥ በሚፈፀሙት ልዩ ልዩ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ምክንያት አል ሲሲን እንደማያነጋግሩ አስታውቀዋል ።

https://p.dw.com/p/1Fbrh
Berlin Pressekonferenz Merkel al-Sisi
ምስል picture-alliance/dpa/von Jutrczenka

[No title]


የግብጹ ፕሬዝዳንት የአብዱል ፈታህ አል ሲሲ የጀርመን ጉብኝት እያወዛገበ ነው ። ሃገራት የሰብዓዊ መብት እንዲያከብሩ አበክራ የምታሳስበው ጀርመን በሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የታሰሩባት ሙት በቃ ብይን የሚወሰንባትና የሚፈፀምባት ሃገር መሪን በእንግድነት መጋበዟ ከውጭም ከሃገር ውስጥም ተቃውሞ አስነስቷል ።የጀርመን ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ኖርቤርት ላሜርት ግብፅ ውስጥ በሚፈፀሙት ልዩ ልዩ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ምክንያት አል ሲሲን እንደማያነጋግሩ አስታውቀዋል ። አንዳንድ ፖለቲከኞች ደግሞ ግብፅ ውስጥ ዲሞክራሲ ሙሉ በሙሉ ከመስፈኑ በፊት የግብፁ መሪ በጀርመን ለይፋ ጉብኝት ባይጋበዙ ይሻል ነበር ሲሉም ተደምጠዋል ።ስለ አልሲሲ የጀርመን ጉብኝት የበርሊኑን ወኪላችንን ይልማ ኃይለ ሚካኤልን ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት በስልክ አነጋግሬዋለሁ ።

ይልማ ኃይለ ሚካኤል

ኂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ