1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አዉሮጳዉያን ባሪያ ፈንጋዮችና የካሳ ጥያቄ

ረቡዕ፣ ሐምሌ 24 2005

ማሕበሩ በተለይ ብሪታንያ፥ ፈረንሳይና ዳች (ወይም ኔዘርላንድን) ካሳ እንዲከፍሉ በሕግ ሊሞግታቸዉ ተዘጋጅቷል።ጠበቆች፥ አንዳድ ሙሑራንና የመብት ተሟጋቾችም የማሕበሩን አቋም እንደሚጋሩ እየተናገሩ ነዉ

https://p.dw.com/p/19Hse
circa 1896: Slaves in chains, guarded by a native Askari, or soldier. (Photo by Hulton Archive/Getty Images)
ምስል Getty Images

 አዉሮጳዉያን ቅኝ ገዢዎችና ተስፋፋዊች አፍሪቃዉያንን እየፈነገሉ በባሪያነት በመሸጥ በመለወጣቸዉ ለዋሉት ግፍ ካሳ እንዲከፍሉ አስራ-አራት የካረቢክ አካባቢ ሐገራት የመሠረቱት ማሕበር ጠየቀ።ማሕበሩ እንደሚለዉ የአዉሮጳ ቅኝ ገዢዎችና ባሪያ ፈንጋዮች በጥንታዊ አፍሪቃዉያን ላይ የፈፀሙት ኢሠብአዊ ግፍ አሁን በካረቢክም ሆነ በተቀረዉ ዓለም ለሚገኘዉ ጥቁር ሕዝብ መደኽየትና ኋላ ቀርነት ዋና ምክንያት ነዉ።ማሕበሩ በተለይ ብሪታንያ፥ ፈረንሳይና ዳች (ወይም ኔዘርላንድን) ካሳ እንዲከፍሉ በሕግ ሊሞግታቸዉ ተዘጋጅቷል።ጠበቆች፥ አንዳድ ሙሑራንና የመብት ተሟጋቾችም የማሕበሩን አቋም እንደሚጋሩ እየተናገሩ ነዉ።የለንደንዋ ወኪላችን ሐና ደምሴ አጭር ዘገባ ልካልናለች።

ሐና ደምሴ

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ