1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አውሮፓና ጀርመን በ2012

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 9 2005

የአባል ሃገራት መሪዎች የ2012 የመጨረሻ ጉባኤያቸውን ባለፈው ሳምንት ካካሄዱ በኋላ ይፋ እንደሆነው የዩሮ ቀውስና መዘዙ ገና አላበቃም ። የተወሰዱት የማስተካከያ እርምጃዎችም በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤት አያመጡም ። በ2013 በደቡባዊ አውሮፓ ሃገሮች የኤኮኖሚ እድገት ዝግመት ሥራ አጥነትንና ድህነትን ያባብሳል የሚል ፍራቻ አለ ።

https://p.dw.com/p/17503
(L to R first row) Slovenian President Danilo Turk, Lithuanian President Dalia Grybauskaite, Italian Prime Minister Mario Monti, Irish Prime Minister Enda Kenny, European Parliament President Martin Schulz, Romanian President Traian Basescu, Cypriot President Demetris Christofias, European Council President Herman Van Rompuy, French President Francois Hollande, European Commission President Jose Manuel Barroso, Greek President Karolas Popoulias, Latvian Prime Minister Valdis Dombrovskis and Dutch Prime Minister Mark Rutte, (L to R second row) Croatian Prime Minister Zoran Milanovic, Danish Prime Minister Helle Thorning-Schmidt, Polish Prime Minister Donald Tusk, Hungarian Prime Minister Viktor Orban, Belgian Prime Minister Elio Di Rupo, Spanish Prime Minister Mariano Rajoy, Swedish Prime Minister Fredrik Reinfeldt, Czech Prime Minister Petr Necas, Slovak Prime Minister Roberto Fico, Portuguese Prime Minister Pedro Passos Coelho, German Chancellor Angela Merkel, Finnish Prime Minister Jyrki Katainen, Austrian Federal Chancellor Werner Faymann, Bulgarian Prime Minister Boyko Borisov, Estonian Prime Minister Andrus Ansip, British Prime Minister David Cameron and Maltese Prime Minister Lawrence Gonzi pose during a family photo at the EU Headquarters on December 13, 2012 in Brussels, on the first day of a two-day European Union leaders. AFP PHOTO / JOHN THYS (Photo credit should read JOHN THYS/AFP/Getty Images)
ምስል AFP/Getty Images
Germany's Chancellor Angela Merkel and France's President Francois Hollande (R) attend a European Union leaders summit in Brussels December 13, 2012. European governments reached a landmark deal on Thursday that gives the European Central Bank new powers to supervise banks, boosting confidence in the single currency bloc as it enters the fourth year of its debt crisis. REUTERS/Francois Lenoir (BELGIUM - Tags: POLITICS BUSINESS)
ምስል Reuters
Italy's EPP party member Silvio Berlusconi talks to the media at the end of the European People's Party summit, ahead of the EU summit in Brussels on Thursday, Dec. 13, 2012. In one whirlwind morning, the European Union nations agreed on the foundation of a fully-fledged banking union and Greece?s euro partners approved billions of euros in bailout loans that will prevent the nation from going bankrupt. (Foto:Yves Logghe/AP/dapd)
ምስል dapd

ከ2 ሳምንት በኋላ አምና ብለን በምንጠራው በጎርጎሮሳውያኑ 2012 አም በአውሮፓ አብዩ ጉዳይ አንደቀደሙት 2 አመታት ሁሉ ዩሮ ለገጠመው ፈተና መፍትሄ ማፈላለግ ነበር ። የአውሮፓ ህብረት መሪዎች በ 2012 ባካሄዷቸው 6 ጉባኤዎች ዋነኛ መነጋገሪያቸው ግሪክ ነበረች ። የእዳ ክምችት እንዲሁም የበጀት ጉድለት ኤኮኖሚዋን ያቃወሰውን ግሪክን ለመታደግ መወስድ የሚገባቸው እርምጃዎች አመቱን ሙሉ ሲያነገጋግሩና ሲያከርክሩ ነው የከረሙት ። በ2012 አጋማሽ ግድም ደግሞ ህብረቱ ግሪክን ከዩሮ ማህበር ሊያስወጣ ነው የሚሉ ወሬዎችም እስከመሰማት ደርሰው ነበር ። ህብረቱ ግን ግሪክን ከጋራው ሸርፍ ዩሮ ተጠቃሚነት የማስወጣት ሃሳብ እንደሌለው ነው የዩሮ ቀጣና አባል ሃገራት ማህበር ፕሬዝዳንት ዦን ክሎድ ዩንከር በወቅቱ ያሳወቁት ። የግሪክ ብቻ ሳይሆን ህብረቱ የታደጋቸው የስፓኝ ና የኢጣልያ እንዲሁም የነርሱ እጣ ይገጥማቸዋል ተብለው የሚያሰጉ የሌሎች የዩሮ ተጠቃም ሃገሮች ይዞታም በአመቱ አሳሳቢነቱ እንደጎላ ነው የዘለቀው ። በተለይ ሙዲስ የተባለው የሃገሮችን የመበደር አቅም ደረጃ የሚያወጣው ዓለም አቀፍ ድርጅት በ2012 እንደ ፈረንሳይ የመሳሰሉ የትላልቅ ኤኮኖሚ አንቀሳቃሽ ሃገሮችን የመበደር አቅም ዝቅ ማደረጉ በእጅጉ አስግቷል ። የህብረቱ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ሆሴ ማኑዌል ባሮሶ 2012ን እንደገመገሙት በተለይም ዝቅተኛ ገቢ ላለው አውሮፓዊ አመቱ ችግር የተሞላበት አመት ነበር ።
«ይህ ዓመት በተለይ በማኅበረሰባችን ለችግር ተጋላጭ ለሆነዉ ወገን በጣም ከባድ ነበር። ሆኖም ግን የችግሩን ሥረ መሠረት እየፈታን ነዉ። የመንግስት ፋይናንስ እየተሻሻለ ነዉ፤ የመወዳደር አቅማቸዉ ዝቅተኛ የሆነ ተፎካካሪዎች ይዞታ እየተሻሻለ ነዉ ፤ የፋይናንስ ዘርፉ ተስተካክሏል ። »
ያም ሆኖ የአባል ሃገራት መሪዎች የ2012 የመጨረሻ ጉባኤያቸውን ባለፈው ሳምንት ካካሄዱ በኋላ ይፋ እንደሆነው የዩሮ ቀውስና መዘዙ ገና አላበቃም ። የተወሰዱት የማስተካከያ እርምጃዎችም በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤት አያመጡም ። መሪዎቹ የአመቱ መዝጊያ በሆነው 6ተኛ ጉባኤያቸው ለቀውሱ ማስተካከያ የአውሮፓ ማዕከላዊ ባንክ የዩሮ ተጠቃሚ አባል ሃገራት ባንኮች የበላይ ተቆጣጣሪ ሊሆን እንደሚችል እንዲሁም ለግሪክ 50 ቢሊዮን ዩሮ አዲስ እርዳታ ለመልቀቅ ተስማምተዋል ። መሪዎቹ የተስማሙባቸው ጉዳዮች የተረጋጋ የኤኮኖሚና የገንዘብ ህብረት ለመፍጠር ወሳኝ እርምጃዎች መሆናቸው ተነግሯል ።

German Chancellor Angela Merkel, center, leaves after an EU summit in Brussels on Friday, Dec. 14, 2012. France and Germany have had more than their share of difference over the past few months, but this week at long last the two countries were able to find a compromise that allowed the European Union to realize a deal on a banking union. (Foto:Michel Euler/AP/dapd)
ምስል dapd
epa03296561 Italian Prime Minister Mario Monti delivers a speech at the Parliament in Rome, Italy, 05 July 2012. Monti urged lawmakers to approve the European Union's fiscal compact and the permanent bailout fund known as the European Stability Mechanism (ESM) before the end of July. EPA/CLAUDIO PERI +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture-alliance/dpa

ይሁንና በ2013 በተለይ በደቡባዊ አውሮፓ ሃገሮች ያጋጥማል ተብሎ የሚያሰጋው የኤኮኖሚ እድገት ዝግመት ሥራ አጥነትንና ድህነትን ያባብሳል የሚል ፍራቻ አለ ። በ2012 የአውሮፓ ህብረት አብይ ትኩረት ከነበረው የዩሮ ቀውስ ወደ ሌሎች የአውሮፓ አበይት ክንውኖች ስንሸጋገር በፈረንሳይ በኢጣሊያና በግሪክ የተካሄዱትን የመንግሥት ለውጦች እናገኛለን ። ፈረንሳይ በ2012 አዲስ ሶሻሊስት መሪ አግኝታለች ።
የፈረንሳይ ሶሻሊስት ፓርቲን ወክለው በምርጫው ለመወዳደር ያቀዱት የቀድሞው የአለም የገንዘብ ድርጅት ፕሬዝዳንት ዶምኒክ ስትራውስ ካን ኒውዮርክ አሜሪካን በወሲብ ቅሉት ተጠርጥረው ለምርመራ ከተያዙ በኋላ ከሃላፊነታቸው ሲወርዱ እጩ ተወዳዳሪ ሆኖ የመቅረብ እቅዳቸውን በመሰረዛቸው ኦሎንድ ተተኩ ። በአጋጣሚው በእጩነት የቀረቡት ኦሎንድም ተፎካካሪያቸውን ኒኮላ ሳርኮዚን አሸነፉ
ኦሎንድ ፈረንሳይን በአሰከፊ የኤኮኖሚ ቀውስ ወቅት የመሩት ሳርኮዚና ሌሎችም የአውሮፓ መሪዎች የሚደጋግሙትን ቁጠባና የበጀት ቁጥጥርን ፣ እድገት በሚለው አዲስ መርህ እንደሚለውጡ ቃል መግባታቸው ለድላቸው ምክንያት ተደርጎ ተወስዷል ። በኢጣልያም እንዲሁ የመንግሥት ለውጥ ተደርጓል ። አወዛጋቢው የኢጣልያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሲልቪዮ ቤርሉስኮኒ በምጣኔ ሃብት ምሁሩና በጠንካራ ተደራዳሪው ማርዮ ሞንቲ የተተኩት በገባደድነው በ2012 ነው ።


የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆኑት የ 68 አመቱ ሞንቲ የመሰረቱት የሽግግር መንግሥት የሚቆየውም ምርጫ እስከሚካሄደበት እስከ 2013 መጀመሪያ ነው ። አመቱን በሙሉ የመላውን አለም ትኩረት ባልተለያት በግሪክም እንዲሁ በአመቱ አጋማሽ በተካሄደ ምርጫ አሸናፊው አዲሱ ዲሞክራቲክ ፓርቲ ከሶሻል ዲሞክራቶችና ከግራ ዲሞክራቶች ፓርቲ ጋር ተጣማሪ መንግሥት መስርቷል ። በግሪክ የተካሄደው ምርጫና ውጤት ግን አበዳሪ መንግሥታትና አለም አቀፍ ድርጅቶች እንዲሁም የአውሮፓ ህብረት በጣላቸው አስገዳጅ የቁጠባ እርምጃዎች ላይ ከህዝቡ በኩል ሲቀርብ የቆየው ተቀውሞ አባሰው እንጂ አላስቆመውም ። በ2012 በግሪክ ኃይል የተቀላቀለባቸው ተቃውሞዎችና የስራ ማቆም አድማዎች ተጠናክረው ሲካሄዱ ነው የከረሙት ። በተገባደደው በ2012 ግሪክን ጨምሮ በበርካታ የአውሮፓ ሃገራት የሚገኙ የሠራተኛ ማህበራት በአንድ ቀን ተቃውሞአቸውን በህብረት አስምተውም ነበር ። ወደ ጀርመን ስናተኩር ደግሞ 2012 ባልታሰበ አጋጣሚ ጀርመን አዲስ ፕሬዝዳንት ያገኘችበት አመት ነበር ። ከግለሰብ በአነስተኛ ወለድ በተበደሩት ገንዘብ ሰበብ ከ2011 አንስቶ ለ 2 ወራት ሲብጠለጠሉ የከረሙት 10ኛው የጀርመን ፕሬዝዳንት ክርስቲያን ቩልፍ ግፊቱ በርትቶባቸው በየካቲት 2012 ሥልጣን ለመልቀቅ ተገደዱ ።

ለ 5 ዓመት የሥልጣን ዘመን ቃለ መሃላ ፈፅመው 2 አመት እንኳን ሳይደፍኑ ከሥልጣን የተሰናበቱት ቩልፍ መጋቢት 2012 በሰብአዊ መብት ተሟጋቹ በዮአሂም ጋውክ
ተተኩ ። በቀደመው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ከቩልፍ ጋር ተወዳድረው ለጥቂት የተሸነፉት ጋውክ ባልጠበቁበት ሁኔታ ለዚህ ሥልጣን በመብቃታቸው መደነቃቸውን በወቅቱ ተናግረው ነበር ።
ጀርመን ሳይታሰብ አዲስ ፕሬዝዳንት ባገኘችበት በ2012 ፣ ከጀርመን በህዝብ ብዛት ከፍተኛውን ቁጥር በሚይዘው በምዕራባዊው በኖርድ ራይን ቬስትፋለን ፌደራዊ ክፍለ ሃገር በተካሄደ ምርጫ የተገኘው ውጤት ለተጣማሪው የጀርመን ገዥ ፓርቲ ክርስቲያን ዲሞክራት ህብረት በጀርመንኛው ምህፃር CDU አስደንጋጭ ነበር ። ግዛቲቱን ተጣምረው የሚገዙት የሶሻል ዲሞክራቶቹ ፓርቲና አረንጓዴዎቹ ፣ CDUን በሰፊ ልዩነት አሸንፈዋል ። ፓርቲያቸው CDU ከ 2 አመት በፊት ካገኘው ውጤት በሩብ መቀነሱን ያስተዋሉት ሜርክል በግዛቱ ሽንፈቱን መራርና የሚያሳምም ነው ያሉት ። CDU በግዛቲቱ በገጠመው ሽንፈት ሰበብ ፓርቲውን ወክለው የተወዳደሩት የፌደራል ጀርመን መንግሥት የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትር ኖርበርት ሮትገን ከክፍለ ሃገሩ የፓርቲ መሪነት ለመልቀቅ ተገደዋል ። ። የCDU ው ሮትገን ብዙም ሳይቆዩ ከአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትርነትም ተሽረዋል ።

የጀርመን መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል አመቱን በድል እያገባደዱ ነው ። ፓርቲያቸውን CDU ን ወክለው በሚቀጥለው አመት ለሚካሄደው የጀርመን አጠቃላይ ምርጫ የሚፎካከሪት ሜርክል ከፍተኛ የህዝብ ተቀባይነትና ጠንካራ ኤኮኖሚ ይዘው ነው የሚጓዙት ። ምንም እንኳን የ 58 አመቷ ሜርክል ጥብቅ የቁጠባ እርምጃ በተጣለበት በግሪክና በስፖኝ ህዝብ ዘንድ ቢጠሉም ለጀርመናውያን መድህን በመሆናቸው ይመሰገናሉ ።

Der vorsitzende der türkischen Gemeinde in Deutschland, Kenan Kolat (r), spricht am Sonntag (09.09.2012) auf dem Bebelplatz in Berlin. Nachdem das Kölner Landgericht die religiöse Beschneidung als Körperverletzung unter Strafe gestellt hat, haben jüdische Organisationen und die Evangelischen Kirche Berlin-Brandenburg zu einer Kundgebung gegen das Urteil unter dem Motto "Auf Messers Schneide: Religionsfreiheit" aufgerufen. Foto: Florian Schuh dpa/lbn +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture-alliance/dpa

ተቃዋሚው SPD በ 2013 የጀርመን አጠቃላይ ምርጫ ፓርቲውን ወክለው የሚወዳደሩ እጩ በይፋ የሰየመው ባለፈው ወር ነበር ። SPD የሰየማቸው እጩ ተወዳዳሪ የቀድሞው የገንዘብ ሚኒስትር ፔር ሽትያንብሩክ ከ2009 አም አንስቶ በተለያዩ አካባቢዎች እየተዘዋወሩ ለሰጡት ገለፃና ላደረጉት ንግግር 1.25 ሚሊዮን ለመቀበላቸው ይቅርታ ለመጠየቅ መገደዳቸው ከወዲሁ የሜርክልን የማሸነፍ እጣ ያሰፋል የሚል ተስፋ ተጥሎበታል ። ያም ሆነ ይህ የምርጫውን ውጤት ከወዲሁ ለመገመት አስቸጋሪ ነው የሚሉት ይበዛሉ ። በአመቱ የምዕራን ጀርመንዋ የኮሎኝ ከተማ ፍርድ ቤት የወንዶች ልጆችን ግርዘት ህገ ወጥና በአካል ላይ ጉዳት ማድረስ ሲል መቃወሙ ከአወዛጋቢ ጉዳዮች አንዱ ሆኖ ነው የከረመው ። የአይሁድ የሙስሊምና የክርስትና እምነት ተከታዮችን ያስቆጣውን ውሳኔ የጀርመን መንግሥትና የጀርመን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውድቅ አድርገውታል ። በአመቱ ውስጥ በጀርመን የስደተኞች መብት ተሟጋቾችንና ተገን ጠያቂዎችና ያስደሰተም ትእዛዝም ተላልፏል ። ጀርመን ለሚኖሩ ስደተኞች የሚሰጠውን ድጎማ ከፍ እንዲደርግ የተላለፈው ትዕዛዝ ። 2012 በአውሮፓ ና በጀርመን ከሞላ ጎደል ይህን ይመስል ነበር ።

ሂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ