አዲሱ የሶማሊያ ዜና አገልግሎት
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 22 2001ማስታወቂያ
የሶማሊያን ወቅታዊ ሁኔታ እየተከታተለ ለተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች ዜና የሚያሰራጭ ገለልተኛ የዜና አገልግሎት ተቋም ትናንት ጀቡቲ ዉስጥ ተከፈተ።SOMINA በሚል የእንግሊዝኛ ምሕፃረ-ቃል የሚጠራዉ ተቋም ከሶማሊያ የሚያሰባስበዉን መረጃ በሶማሊያኛ፥ በእንግሊዝኛ እና በሌሎችም ቋንቋዎች ለራስዋ ለሶማሊያና ለአለም አቀፍ መገናኛ ዘዴዎች ያሰራጫል።በሶማሊያዉያን ጋዜጠኞች የሚመራዉን ተቋም ፓሪስ የሚገኘዉ ጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት-ድንበር የለሽ ዘጋቢዎች፥ ዶሐ-ቀጠር የሚገኘዉ ለመገናኛ ዘዴዎች ነፃነት የሚሟገተዉ-ማዕከልና በሶማሊያ ጋዜጠኞች ሕብረት የሚረዳ ነዉ።ነጋሽ መሐመድ ዝር ዝሩን አጠናቅሮታል።
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ