1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አዲሷ የአፍሪቃ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር

ሰኞ፣ ሐምሌ 9 2004

የአፍሪቃ ህብረት የደቡብ አፍሪቃ ሀገር አስተዳደር ሚንስትር ንኮሳዛና ድላማኒ ዙማን ትናንት ማታ የህብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ። ድላማኒ ዙማ የመጀመሪያ ሴት የህብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ናቸው።

https://p.dw.com/p/15Yfv
South African Home Affairs Minister Nkosazana Dlamini-Zuma addresses the media during the leaders meeting at the African Union (AU) in Addis Ababa July 15, 2012. African leaders brought together the presidents of feuding neighbours Sudan and South Sudan on Saturday and fleshed out a plan for military intervention in northern Mali where they said al Qaeda-linked rebels threatened the continent's security. REUTERS/Tiksa Negeri (ETHIOPIA - Tags: SOCIETY POLITICS)
ምስል Reuters

ህብረቱ ባለፈው ጥር ባካሄደው ጉባዔው ለኮሚሽኑ ሊቀመንበርነቱ ሥልጣን በተወዳዳሪነት በቀረቡት ካለፈው 2008 ዓም ወዲህ ኮሚሽኑንን በሊቀመንበርነት በመሩት ዣን ፒንግ እና በንኮሳዛና ድላማኒ ዙማ መካከል ለመምረጥ ያደረገው ጥረቱ ሁለቱም ዕጩዎች ሁለት ሦስተኛውን ድምፅ ባለማግኘታቸው ሳይሳካ ቀርቶ፡ ዣን ፒንግ ሥልጣኑን ያለፉትን ስድስት ወራት በተጠባባቂነት እንደያዙ እንዲቆይ ወስኖ እንደነበር አይዘነጋም። አዲሷ ሊቀመንበር በመላው አህጉር ሰላም የሚሰፍንበትን ሂደት የማበረታታት፡ በማሊ፡ በዴሞክራቲክ ሬፓብሊክ ኮንጎ የቀጠለውን የፖለቲካ ቀውስ የሚያበቃበትን መፍትሔ የማፈላለግ፡ እንዲሁም በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን ዕርቀ ሰላም የሚወርድበትን ጥረት የማጠናከር ሥራ ይጠብቃቸዋል። ካለፈው ሰኞ ወዲህ በመካሄድ ላይ ያለው የአፍሪቃ ህብረት ጉባዔ ዛሬ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

African Union Commission chairman Jean Ping arrives for the 18th African Union (AU) Summit in the Ethiopia's capital Addis Ababa, January 29, 2012. REUTERS/Noor Khamis (ETHIOPIA - Tags: POLITICS HEADSHOT)
ምስል Reuters

አርያም ተክሌ

ነጋሽ መሀመድ