ኢትዮጵያዉያን ተጓዦችና የአፍሪቃ እግር ኳስ ዋንጫ
ረቡዕ፣ ጥር 1 2005ማስታወቂያ
ኢትዮጵያዉያን የግል ባለሐብቶች ያደራጁት የተጓዦች ቡድን በቅርቡ ደቡብ አፍሪቃ የሚደረገዉን የአፍሪቃ እግር ኳስ ግጥሚያን ለመመልከት ከኢትዮጵያ በመኪና ወደ ደቡብ አፍሪቃ ጉዞ ጀመረ።ባለሐብቶች፥ ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች የሚገኙበት አስራ-ሰባት አባላት ያሉት ቡድን፤ የቡድኑ አስተባባሪ እንዳስታወቁት፤ ስፖርት፥ ቱሪዝምና ሠላም የሚል ዓላማ ያነገበ ነዉ።ቡድኑ በደቡብ አፍሪቃዉ ጨዋታ የሚካፈለዉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የሚያደርጋቸዉን ግጥሚያዎች ይመለከታል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪቃ ዋንጫ ግጥሚያ ላይ ሲካፈል ከሰሳላ አንድ ዓመት ወዲሕ የዘንድሮዉ የመጀመሪያዉ ነዉ።ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝር ዘገባ አለዉ
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ