ኤቦላ እና የአውሮጳ ኅብረት ርዳታ
ማክሰኞ፣ መስከረም 20 2007ማስታወቂያ
ዩኤስ አሜሪካ በኤቦላ የተከሰተባቸው የምዕራብ አፍሪቃ ሀገራት ወረርሽኙን ለመታገል በጀመሩት ዘመቻ ላይ የሚረዱ 3,000 ወታደሮችን እንደምትልክ ከፍተኛ የዋይት ሀውስ ቤተ መንግሥት ባለሥልጣናት መግለጻቸው ይታወሳል። ወታደሮቹ ኤቦላ ወደተስፋፋባቸው ላይቤርያ፣ ሲየራ ልዮን እና ጊኒ በመሄድ በዚያ እያንዳንዳቸው 100 አልጋዎች የሚኖሩዋቸው 17 ክሊኒኮችን በመገንባት እና እስከ 500 የሚጠጉ የጤና መኮንኖችን በማሠልጠኑ ተግባር ላይ እንደሚሠማሩ ተገልጾዋል።የኤቦላን ስርጭት ለመቆጣጠር በተጀመረው ጥረት ላይ የአውሮጳ ኅብረት አስተዋፅዖስ ምን ይመስላል?
ቤርንት ሪገርት
ይልማ ኃይለሚካኤል
አርያም ተክሌ