1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

እግር ኳስና ዘረኝነት

ሐሙስ፣ ሰኔ 7 2004

በመካሄድ ላይ ባለው የአውሮፓ እግር ኳስ ዋንጫ አንዳንድ እግር ኳስ አፍቃሪዎች የሚፈጽሟቸው ዘረኛ ድርጊቶች በቀላሉ መታለፍ እንደማይገባቸው Farenet በመባል የሚጠራው ድርጅት አስታወቀ ። ዘረኝነትንና አድልዎን የሚቃወሙ ቡድኖችን ያያሰባሰበው

https://p.dw.com/p/15EpF
German and Brazilian players together hold a banner against racism prior to the Confederations Cup semi final between Germany and Brazil in Nuremberg, Germany, Saturday, June 25, 2005. (AP Photo/Thomas Kienzle)
ምስል AP

በመካሄድ ላይ ባለው የአውሮፓ እግር ኳስ ዋንጫ አንዳንድ እግር ኳስ አፍቃሪዎች የሚፈጽሟቸው ዘረኛ ድርጊቶች በቀላሉ መታለፍ እንደማይገባቸው Farenet በመባል የሚጠራው ድርጅት አስታወቀ ። ዘረኝነትንና አድልዎን የሚቃወሙ ቡድኖችን ያሰባሰበው የ Farenet ሃላፊ እንደሚሉት በአውሮፓ ተደጋግሞ የሚደርሰውን ይህን አስነዋሪ ተግባር ለማስቀረት ከሚወሰዱ የቅጣት እርምጃዎች በተጨማሪ የአስተሳሰብ ለውጥ ለማምጣት ትምህርት መሰጠትም ችግሩን በዘላቂነት ለማስወገድ ይረዳል ። ። ያነጋገረቻቸው ሂሩት መለሰ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅራለች
በዘንድሮው የአውሮፓ እግር ኳስ ሻምፕዮና ተጫዋቾች በቆዳ ቀለማቸው ምክንያት በኳስ ሜዳ በግልፅ ዘረኛ ጉንተላዎች ደርሰውባቸዋል ። ከቼክ ሪፐብሊካዊት እናቱና ከኢትዮጵያዊ አባቱ የተወለደው የቼኩ አጥቂ ቴዎዶር ገብረሥላሴ ይህ ካጋጠማቸው ተጫዋቾች አንዱ ነው ። የቼክ ቡድን ከሩስያ ጋራ ባካሄደው ጨዋታ የተሰለፈውን ቴዎዶር ወይም ቲዮን የሩስያ ደጋፊዎች በጦጣ መሰል ድምፅ

Czech Republic's team players celebrate scoring during their Group A Euro 2012 soccer match against Greece at the City stadium in Wroclaw June 12, 2012. REUTERS/Kacper Pempel (POLAND - Tags: SPORT SOCCER)
ምስል Reuters

ተንኩሰውታል ። የሆላንድ ቡድን አባላትም ፖላንድ ውስጥ በሥለጠና ላይ ሳሉ ተመሳሳይ ጉንተላ ገጥሟቸዋል ። በእግር ኳስ ሜዳ የሚፈፀሙ እነዚህን መሰል አሳፋሪ ተግባራት የሚከታተለው Farenet የተባለው ድርጅት ሃላፊ ፕያራ ፓወር ይህ ለዚህን መሰሉ ድርጊት በማስረጃነት መያዙን ተናግረዋል ።
« በአሁኑ ጨዋታ ገብረሥላሴ ላይ ዘረኝነትን የሚያንፀባርቅ እኩይ ትንኮሳ መድረሱን ከታዛቢዎቻን አንዱ ተመልክቷል ገብረሥላሴም በቼክ መገናኛ ብዙሃን የጦጣ መሰል ድምፅ መስማቱን አረጋግጧል ። የሩስያ ደጋፊዎች ደግሞ ይህን አስተባብለዋል ። ይህም ለአውሮፓ አገሮች የእግር ኳስ ማህበር UEFA አንድ ማስረጃ ነው ። »
ፓወር የሚመሩት ፌርኔት በእግር ኳስ ሜዳዎች የሚፈፀሙ ዘረኛ ድርጊቶችን መከታተል ከጀመረ 8 ዓመት ይሆነዋል ። እርሳቸው እንደሚሉት በአውሮፓ እግር ኳስ ሜዳዎች ዘረኛ ድርጊቶች መፈፀማቸው አዲስ አይደለምና አያስገርምም ። ግን የአውሮፓ እግር ኳስ ዋንጫን በሚያህል ትልቅ ጨዋታ ላይ መድረሱ አሳፋሪ ቢሆንም ጉዳዩ እንዲተኮርበት ደግሞ ጥሩ አጋጣሚ ሆኗል ።
« አስደንጋጭ በጣም አሳዛኝ ነበር ። በዓለም ፊት ትልቁ የአውሮፓ እግር ኳስ ጨዋታ እየተካሄደ ዓለም ሁሉ በሚከታተልበት ወቅት ነው የተፈፀመው ። እርግጥ ነው በአውሮፓ በደቡብ አሜሪካና በሌሎችም የእግር ኳስ ጨዋታዎች ና ስፖርታዊ ውድድሮች የሚታየው ይህ ትልቅ ችግር ትኩረት እንዲሰጠው ያደርጋል ። »


የፌርኔት ሁለት ነፃ ታዛቢዎች በእያንዳንዱ ጨዋታ እየተገኙ በቴዎዶር ገብረ ሥላሴ ላይ የደረሰውን መሰል ዘረኛ ድርጊቶች በመመዝገብ ጨዋታውን በሃላፊነት ለሚመራው የአውሮፓ አገሮች የእግር ኳስ ማህበር ዘገባ ያቀርባሉ ። ድርጅቱ ከዚህ ሌላ በየሃገሩ የሚታዩትን የውጭ ዜጎች ጥላቻ ብሔረተኝነትን ና የቀኝ አክራሪነት ምልክቶችንም ያሳውቃል ።
የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር በደጋፊዎቹ ስርዓት የጎደለው ድርጊት በሩስያ ፌደሬሽን ልይ የ120 ሺህ ዮሮ ቅጣት ና የነጥብ ቅነሳ እርምጃ ወስዷል ። ሆኖም ፓወር ቅጣት ብቻውን ውጤት አያመጣም ነው የሚሉት ።
«በኛ እምነት ስህተት ከተፈፀመ ጉዳዩ የሚመለከተው ወገን ቅጣት እዳለ ለማሳወቅ እርምጃ መውሰድ አለበት ይህ ይሰራል በረዝም ጊዜ ደግሞ በማስተማር ህዝቡ የአስተሳሰብ ለውጥ እንዲያመጣ ስፖርት በአውሮፓ ባህል እንደመሆኑ ህዝቡ አውሮፓ የተለያዩ ባህሎች የሚገኙባትክ ክፍለ ዓለም መሆኗን እንዲቀበል መሥራት ያስፈልጋል ። ረዥም ጊዜ ይወስዳል እንጂ ለውጥ ይመጣል »

Vor dem Olympiastadion Kiew ist ein übergroßer Fußball mit dem Logo der UEFA Euro 2012 am Freitag (20.04.2012) in Kiew in der Ukraine aufgestellt. Es ist ein Austragungsort für Spiele der UEFA Euro 2012 Fußball-Europameisterschaft Polen Ukraine. Es ist für das Endspiel vorgesehen, es werden hier 3 Vorrundenspiele sowie ein Viertelfinale stattfinden. Foto: Jens Kalaene
ምስል picture-alliance/dpa

ሂሩት መለሰ

ነጋሽ መሀመድ