1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከሊቢያ ለጉዞ የተዘጋጁ ስደተኞች

ዓርብ፣ ጥቅምት 1 2006

ኣንዳንድ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ስደተኞች ታጉረው ከሚገኙበት ወይንም ተደብቀው ጀልባ ከሚጠባበቁበት የትሪፖሊ ማጎሪያ ቤት ለዶቸቬሌ አነጋግሯቸዋል።

https://p.dw.com/p/19yLS
ምስል picture-alliance / abaca

እንደተናገሩትም በሱዳን በኩል ኣድርገው ሊቢያ እስኪደርሱ በዚህ ረጅም የበረሃ ጉዞ የደረሰባቸውስቃይ ሳያንሳቸው ኣሁንም የባህር ላይ ኣሰቃቂ ጉዞ ይጠብቃቸዋል። በእርግጥ ስደተኞቹ እንደሚሉት ያ ከሁለት መጥፎ ይሻላል ብለው የመረጡት የተሻለ መጥፎ በመሆኑ እዚያው ሊቢያ ውስጥ በፖሊሶች የሚደርስባቸውን ዘረፋ እና እስራት ነው ይበልጥ የሚያማርሩት።

ከ UNHCRየጀኔቫ ቢሮ ቃል ኣቀባዩ ሚ/ር ዳን ሚክኖኣፓኔ እንደሚሉት ለችግሩ መፍትሄ ለመሻት የሚደረገው ጥረት ማነጣጠር ያለበት መነሻው ላይ ነው።


ይህ ግን ጊዜ የሚፈጅ በመሆኑ ሚ/ር ዳን እንደሚሉት የኣውሮፓ ህብረት እና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ስደተኞች ተገን የሚጠይቁበትን ቦታ እና የሚያገኙበትን ሁኔታ እንደገና ሊመረምሩ ይገባል። ከዚሁ ጎን ለጎን ደግሞ የባህር ላይ ቁጥጥሩም በእርግጥ ሊጠናከር ይገባል ባይ ናቸው ሚ/ር ዳን።

Italien Lampedusa Flüchtlinge Libyen Tunesien
ምስል picture alliance / dpa

ጃፈር ዓሊ

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ