ከስዑዲ ዐረቢያ ለመመለስ የተዘጋጁ ኢትዮጵያውያን እንግልት፣
ማክሰኞ፣ ነሐሴ 18 2002ማስታወቂያ
ባሉ ኢትዮጽያውያን ላይ ሐሩሩ እጅግ አይሎባቸዋል።
በእስረኛ ብዛት ሳቢያ በሚፈጠረው መተፋፈግም ብዙዎቹ፣ ለከፋ ተላላፊ በሺታ መጋለጣቸውን ታሳሪዎች ይገለጻሉ፡፡ ሴቶቹ ታሣሪዎች፤ መፍትሄ ያገኙ ዘንድ፣ ጠባቂ ፖሊሶችን ሲጠይቁ ፤
ችግራቸው ሊፈታ የሚችለው በሃገራቸው መንግስት በኩል በመሆኑ፤ እነርሱ ምንም ማድረግ እንደማይችሉ ነው የሚገልጹላቸው።
የሳውዲ ሰብአዊ መብት ማህበር ፣ የጂዳና የመካ አካባቢዎች ሃላፊዎችም ፣ ችግሩን የሳውዲ መንግስት ሳይሆን የስደተኞቹ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከታቸው የተለያዩ ሃገራት ቆንስሎችና የኤምባሲ መሥሪያ ቤቶች ድክመት፣ ነገሩን ውስብስብ አድርጎታል ሲሉ ይገልጻሉ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ምንም እንኩዋን በእስር ቤት ያለው ሁኔታ አስክከፊ ነው ቢባልም ፣ ከድልድይ ስር ሆነው እጃቸውን ለፖሊስ ለመስጠት ከተጠለሉበት ድልድይ ፣ የመንግስታቸው እርዳታ ተነፍጎዋቸው በርካታ ችግር ሲያጋጥማቸው የተስተዋሉት ኢትዮጽያውያን ባሳለፍነው ሳምንት መገባደጃ የመጉዋጉዋዣ ሰነድ ከሌላቸው ውጭ፣ ሰነድ ያቀረቡ ኢትዮጽያውያን በአብዛኛው በፖሊስ ተይዘው ማቆያውን እስር ቤት እንደተቀላቀሉ ታውቋል፡፡
ነቢዩ ሲራክ
ሒሩት መለሰ