1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በርካቶች ተፈናቅለዋል

ረቡዕ፣ መስከረም 3 2010

በግጭቱ መንስኤ በቀጠለው ተቃውሞም ዛሬ ከድሬዳዋ ከሐረር እና ጅግጅጋ ይነሱ የነበሩ አገር አቋራጭ አውቶብሶች እና ሚኒባሶች አገልግሎት አቋርጠዋል።

https://p.dw.com/p/2juNt
20.06.2013 DW Online Karten Basis Aethiopien spanisch

ከድሬዳዋ እስከ ጅግጅጋ ያለው መንገድ ተዘግቷል።

 

በሶማሌ እና በኦሮምያ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭት መንስኤ ሰዎች መፈናቀላቸው ተሰማ። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ከአካባቢው ነዋሪዎች እንደሰማው የተፈናቀሉት ቁጥር ከ1 ሺህ ሊበልጥ ይችላል። በግጭቱ መንስኤ በቀጠለው ተቃውሞም ዛሬ ከድሬዳዋ ከሐረር እና ጅግጅጋ ይነሱ የነበሩ አገር አቋራጭ አውቶብሶች እና ሚኒባሶች አገልግሎት አቋርጠዋል። ከድሬዳዋ እስከ ጅግጅጋ ያለው መንገድም ተዘግቷል። የአዲስ አበባውን ዘጋቢያችንን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔርን ኂሩት መለሰ አነጋግራዋለች።  ዮሐንስ በቅድሚያ ትናንት እና ዛሬ በየከተሞቹ ስለሆነው የሰማውን ይገልጽልናል። 

ዮሐንስ ገብረ ዝግዚአብሔር

ኂሩት መለሰ 
አርያም ተክሌ