1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከቀዉስ ያልወጣችዉ ሶማሊያ

ሐሙስ፣ ጥር 7 2001

በሶማሊያ ለሁለት ዓመታት የሰነበተዉ ኢትዮጵያ ወታደራዊ ኃይል መቃዲሾ ከሚገኙ የጦር ሰፈሮቹ የመጨረሻዉ ቡድን መልቀቁን ዘገባዎች እየገለጡ ነዉ።

https://p.dw.com/p/GZCP
ታጣቂዎች በሶማሊያ
ታጣቂዎች በሶማሊያምስል AP

የአፍሪቃ ህብረት የሰላምና የፀጥታ ኮሚሽነርን ጨምሮ በርካታ ታዛቢዎች የወታደሮቹ መዉጣት በሶማሊያ የፀጥታ ክፍተትን ፈጥሮ አገሪቱን ከከረመባት ዉጥንቅጥ እንደሚዘፍቃት ስጋታቸዉን ያሰማሉ። በአንፃሩ የኢትዮጵያ ወታደሮች መዉጣት ጦርነት እንዲያከትም፤ እርቅ እንዲሰፍን ይረዳል የሚሉም አልጠፉም።