1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከድንበር የተጠለፉ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ

ሐሙስ፣ ግንቦት 9 2004

የኢትዮጵያ መንግሥት ከኤርትራና ኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ በኤርትራ ታፍነው ተወስደዋል ያላቸውን ኢትዮጵያውያንን ለማስለቀቅ ሙከራውን መቀጠሉን አስታወቀ ። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ዲና ሙፍቲ ዛሬ እንዳሉት መንግሥት ችግሩን

https://p.dw.com/p/14xAn
ምስል AP Graphics/DW


የኢትዮጵያ መንግሥት ከኤርትራና ኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ በኤርትራ ታፍነው ተወስደዋል ያላቸውን ኢትዮጵያውያንን ለማስለቀቅ ሙከራውን መቀጠሉን አስታወቀ ። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ዲና ሙፍቲ ዛሬ እንዳሉት መንግሥት ችግሩን ለመፍታት ጥረቱን አላቋረጠም ። የኤርትራ መንግሥት በበኩሉ ክሱን አስተባብሏል ። የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ፀሃዬ ፋሲል የኢትዮጵያ ውንጀላ የተለመደና ፣ መንግሥት ውስጣዊ ችግሮቹ ላይ እንዳይተኮር የሚጠቀምበት ዘዴ ነው ሲሉ ተናግረዋል ። ሁለቱንም ያነጋገረችው ሂሩት መለሰ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅራለች
የኢትዮጵያ መንግሥት ጎረቤት ኤርትራ ዜጎቼን አፍና ወስዳለች ሲል በይፋ ከከሰሰ አንድ ወር አልፏል ። የሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ አንዳንድ ነዋሪዎችና አንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ፣ ከአካባቢው ወጣቶች መጠለፋቸው ከተነገረበት ከዚያን ጊዜ ወዲህም አፈናው መቀጠሉን ይናገራሉ። ይሁንና የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ዲና ሙፍቲ የተጠለፉት ሰዎች ቁጥር ከዚህ ቀደም ከተገለፀው የተለየ እንዳልሆነ ነው ያስረዱት


ኤርትራ ወጣት ኢትዮጵያውያንን ክድንበር አካባቢ አፍና ወሰደች መባሉን ግን ሃሰት ስትል ነው ያስተባበለችው ። የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ፀሃዮ ፋሲል
ኢትዮጰያ አፈናው በኤርትራ መንግሥት ለመከናወኑ መረጃ አለኝ ትላለች  ።
የኤርትራ መንግሥት ወጣቶቹን ስለማፈኑ ኢትዮጵያ የምታቀርበው ማስረጃ ምንድነው ተበለው አቶ ዲና ለተጠየቁት ሲመልሱ

Blick über die Häuser von Asmara, Independence Avenue
ምስል picture-alliance/ dpa


የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፀሃዮ እንደሚሉት ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ይህን መሰሉ ክስ ሲሰነዘር  አዲስ አይደለም ። ኢትዮጵያ ይህን የምታደርገውም በርሳቸው አባባል የውስጥ ችግሮችዋን ወደ ሌላ ወገን ለማላከክ ነው ።
ኤርትራ ይህን ስትል የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ የተያዙትን ዜጎች ለማሰለቀቅ 3 አብይ ስልቶችን እየተከተልኩት ነው ይላል ። አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
አቶ ፀሃዮ ፋሲል ግን ምንም በሌለበት ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ሊኖር አይችልም ነው የሚሉት
ድምፅ 

Meskal Square im Zentrum der äthiopischen Hauptstadt Addis Abeba
ምስል picture alliance/dpa

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ