1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኩረጃ በተንቀሳቃሽ ስልኮች

ዓርብ፣ ሚያዝያ 4 2005

ት/ቤት ውስጥ በፈተና ወቅት በቁራጭ ወረቀት ላይ መልስ ፅፎ መቀባበል ጊዜ ያለፈበት ይመስላል። አሁን የዘመኑን ተንቀሳቃሽ ስልክ ተጠቅሞ ከአንዱ የክፍል ጠርዝ የሌላኛው ጠርዝ ድረስ መልዕክት በመላላክ ይኮረጃል አልያም በስልኩ ኢንተርኔት ውስጥ ተገብቶ መልስ ይፈለጋል። ይህ የሚደረገው በበለፀገው አለም ብቻ አይደለም። በኢትዮጵያም ጭምር እንጂ።

https://p.dw.com/p/18EOd
ምስል Fotolia/lassedesignen

ትምህርት ቤት ውስጥ በፈተና ወቅት በቁራጭ ወረቀት ላይ መልስ ፅፎ መቀባበል ጊዜያለፈበት ይመስላል። አሁን የዘመኑን ተንቀሳቃሽ ስልክ ተጠቅሞ ከአንዱ የክፍል ጠርዝ የሌላኛው ጠርዝ ድረስ መልዕክት በመላላክ ይኮረጃል አልያም በስልኩ ኢንተርኔት ውስጥ ተገብቶ መልስ ይፈለጋል። ይህ የሚደረገው በበለፀገው አለም ብቻ አይደለም። በኢትዮጵያም ጭምር እንጂ። « ኩረጃ በተንቀሳቃሽ ስልኮች» የዛሬው የወጣቶች አለም ርዕስ ነው።

Der Schüler Jonas (l) und die Schülerin Desiree (r) der Staudinger-Gesamtschule in Freiburg telefonieren auf dem Pausenhof der Schule mit ihrem Handy (Archivfoto vom 20.03.2001). Nach den Osterferien gilt an der Volksschule in Altusried (Oberallgäu) ein Handy-Verbot. Die Grund- und Hauptschüler dürfen ein Mobiltelefon nicht einmal ausgeschaltet mit in die Klassenzimmer nehmen. Das Kultusministerium ist mit dieser in Bayern einmaligen Regelung nicht einverstanden. Aus Sicherheitsgründen solle man den Kindern gestatten, ihr Handy mitzuführen, wenn es ausgeschaltet ist. Die Altusrieder Schule will dennoch an ihrem grundsätzlichen Verbot festhalten. Foto: Rolf Haid dpa/lby
በት/ቤት ውስጥ የተማሪዎች ስልክ መጠቀም እየተለመደ ነው።ምስል picture-alliance / dpa/dpaweb

ኩረጃ ከትምህርት ቤት ጨርሶ የሚጠፋ አይመስልም። ይጠፋልም ብሎ ለመገመት ያዳግታል። ግፋ ቢል የኩረጃ መንገዱ ከጊዜ ወደ ጊዜ ይቀያየር ይሆናል። የዘመኑ ኩረጃ ቴክኖሎጂ ባመጣው የተንቀሳቃሽ ስልክ ሆኗል።

ስማርት ፎን በመባል የሚታወቁት እጅግ ዘመናዊ ስልኮች በተስፋፉባቸው ሀገራት ፤ በትምህርት ቤት ፈተና ወቅት፤ኩረጃን እጅግ ቀላል አድርጎታል። መልስ መላላክ፣ ገፆችን ፎቶ አንስቶ በመግባት ከስልክ ላይ መኮረጅ፣ ያልታሰበ ጥያቄም ከሆነ በፈጣኑ ኢንተርኔት እንደ ዊኪፒዲያ ያሉ ገፆች ላይ መልሱ ይፈለጋል። ኩረጃ በተንቀሳቃሽ ስልኮች ኢትዮጵያ ውስጥ ምን ያህል ተስፋፍቷል? ሁለት የኮሌጅ ተማሪዎች ያጫወቱን አለ።

ስልክን የመሰለ ቴክኖሎጂ ተማሪዎች ጋ መድረሱ መልካም ቢሆንም ያለአግባቡ እየዋሉ እንደሆነ አንዳንድ አስተማሪዎችም ያውቃሉ። ነፃነት በአንድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም አስተማሪ ናት። 31 አመቷ ነው። በክፍል ውስጥ አስተማሪ እና ተማሪን ስለሚያጋጨው የተንቀሳቃሽ ስልክ ጉዳይ በሚገባ ታውቀዋለች። እሷ እና የስራ ባልደረቦቿ ስለሚገጥማቸው ነግራናለች።

ከውጭው ሀገር የመጣ እንደ ተንቀሳቃሽ ስልክ ያለ ተክኖሎጂ ወጣቱ ዘንድ መድረሱ ጥሩ ቢሆንም አልፎ አልፎ በአንዳንድ ተማሪዎች ዘንድ ያለአግባብ እየዋለ ነውና በተለይ የመምህራንን ጥብቅ ቁጥጥር ይሻል። ሙሉውን ዝግጅት ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።

ልደት አበበ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ