1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ወስባዊ ጥቃት በህንድ

ዓርብ፣ ታኅሣሥ 26 2005

የ 23 ዓመቷ ህንዳዊት የህክምና ተማሪ ነበረች ። ያለፈው ቅዳሜ በሚያሳዝን ሁኔታ ህይወቷ አልፏል።

https://p.dw.com/p/17EJs
Kerzenmeer am Jantar Mantar für das Opfer der Vergewaltigung am 16. Dezember. Copyright: DW/Sandra Petersmann Januar, 2012, Neu Delhi
ምስል DW/S. Petersmann

ከሶስት ሳምንት በፊት በወጣቷ ላይ ስድስት ወንዶች የቡድን ወሲባዊ ጥቃት ፈፅመው በብረት ደብድበው በመጓዝ ላይ ከነበረችበት አውቶብስ ወርውረው ጥለዋታል። ወጣቷ በህክምና እየተረዳች ብትቆይም ከደረሰባት ውስባዊ የአካል ጉዳት ማገገም ግን አልቻለችም።

Betende Frauen am Jantar Mantar. Copyright: DW/Sandra Petersmann Januar, 2012, Neu Delhi
ምስል DW/S. Petersmann

ህንድ ውስጥ ለዓመታት የሴቶችን መብት ለማስከበር የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች በመጣር ላይ ይገኛሉ። ሆኖም ዛሬ በሴቶች ላይ በርካታ ጥቃት ይደርሳል እንዲሁም የእኩልነት መብታቸው ይረገጣል። የወጣቷ አሟሟት በአለም ዙሪያ ከፍተኛ የመገናኛ ብዙኃን ሽፋን ያግኝ እንጂ በህንድ እኢአ በ2011 ዓም ብቻ ከ24 000 በላይ አስገድዶ የመድፈር ጥቃት ተመዝግበዋል። ይህ አሃዝ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ በ2000 መጨመሩ ታይቷል። ይህን ፆታዊ ጥቃት ከሚያደርሱት ወንጀለኞች መካከል በቁጥጥር ስር የሚውሉት ግን ከአራቱ ወንዶች መካከል አንዱ ወንጀለኛ ብቻ ነው።

የህንድ ፖሊስ እንዳስታወቀው በፆታ ጥቃት ህይወቷ የጠፋውን የ 23 ዓመት ወጣት ጉዳይ በጥብቅ እየተከታተለ ይገኛል። በትናንትናው ዕለት ፖሊስ አስገድዶ በመድፈር የተጠረጠሩ ስድስት ሰዎችን ነፍስ በማጥፋት ወንጀል ለፍርድ አቅርቧል። ይህ ሲሆን በሌላ በኩል በርከት ያሉ የህግ ባለሙያዎችም ከዋና ከተማዋ ፍርድ ቤት ፊት ለፊት በመሰለፍ ሴቶች ላይ የሚፈፀም ፆታዊ ጥቃት እንዲገታ ጠይቀዋል።

Indian women lawyers shout slogans against police and the government outside the District Court complex where a new fast-track court was inaugurated Wednesday to deal specifically with crimes against women, in New Delhi, India, Thursday, Jan. 3, 2013. Indian police were preparing Thursday to file rape and murder charges against a group of men accused of sexually assaulting a 23-year-old university student for hours on a moving bus in New Delhi. The Dec. 16 attack on the woman, who later died of her injuries, has caused outrage across India, sparking protests and demands for tough new rape laws, better police protection for women and a sustained campaign to change society's views about women. (Foto: Manish Swarup/AP/dapd)
በመዲና ኒው ዴህሊ የተደረገ ተቃውሞምስል dapd

«የህግ ባለሙያዎች በጉዳዩ በጣም አዝነዋል። የህግ ግንዛቤዉ አለ፤ ወንጀሉ ምን ያህል ከብዶ እንደተፈፀመ እንረዳለን። በሀገራችን ዛሬም ቢሆን ሴቶች ደህንነታቸዉ አልተረጋገጠም። እኛ ወንዶች ነን ሆኖም ሴቶቻችን ደህንነታቸዉ እንዲከበር እንፈልጋለን።»

ጉዳዩ የህግ ባለሙያዎችን ብቻ ሳይሆን በርካታ የሀገሪቱ ህዝብንም አስቆጥቷል። የወጣቷን አሳዛኝ ዜና ታሪክአለም ዳንኤል ከአዲስ አበባ በመገናኛ ብዙኋን ተከታትላዋለች። አስተያየቷን አካፍላናለች። እንዲሁም ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚታየው አስገድሶ የመድረር ጉዳይ በተመለከተም በፌስ ቡክ የተለያዩ አስተያየቶች ደርሰውናል።

በህንድ የሞት ቅጣት እንብዛም የተለመደ እንዳልሆነ እና በጣም አስከፊ ወንጀሎች ሲደርሱ ብቻ በተግባር ላይ እንደሚውል ነው ዘገባዎች የሚያመላክቱት። በህንድ እኢአ ከ 2004 ዓም ከተበየነ አንድ የሞት ቅጣት በኋላ እኢአ 2008 ሞምባይ ውስጥ የፍንዳታ ጥቃት በጣለ ዜጋ ላይ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ዳግም የሞት ቅጣቱ ተግባራዊ ሆኖ ነበር።

ዛሬ በህንድ ሰሜን ምስራቃዊ ግዛት 600 ጊታር ተጫዋጮች ሟቿን ወጣት « ኢማጅን » በተሰኘው የጆን ሌንን ዜማ ዘክረዋታል። ከሙዚቃ አዘጋጆቹ አንዷ ሶናም ቡቲያ ይህንን ዜማ የመረጡበት ምክንያት ስለ ተስፋ፣ ነፃነት እና ቃል ኪዳንን ስለሚያወሳ ነው ብለዋል።

አስገድዶ መድፈርን በተመለከተ የተቀናበረውን ዘገባ ማድመጥ ይችላሉ።

ልደት አበበ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ