1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ወጣት ሴቶች በሳውዲ ዓረቢያ

ዓርብ፣ መስከረም 4 2005

በርካታ ኢትዮጵያውያን ሴቶች በየጊዜው የተሻለ ህይወት ፍለጋ ወደ አረብ ሀገር ይጓዟሉ። በርግጥ እዚያ ኢትዮጵያ ውስጥ በቤት ሰራተኝነት ከሚያገኙት የበለጠም ይከፈላቸዋል። ግን፤ ኑሮ በአረብ አገር በጣም ከባድ እንደሆነ፤ በተለይ ሄደው ያዩት በተደጋጋሚ ይናገራሉ።

https://p.dw.com/p/168Fr
Saudi women board a taxi in Riyadh, Saudi Arabia, Tuesday, May 24, 2011. A Saudi woman was arrested for a second time for driving her car in what women's activists said Monday was a move by the rulers of the ultraconservative kingdom to suppress an Internet campaign encouraging women to defy a ban on female driving. Manal al-Sherif and a group of other women started a Facebook page called "Teach me how to drive so I can protect myself," urging authorities to lift the ban and posted a video clip last week of al-Sherif behind the wheel in the eastern city of Khobar. The page was removed after more than 12,000 people indicated their support for its call for women drivers to take to the streets in a mass drive on June 17. (ddp images/AP Photo/Hassan Ammar) // Eingestellt von wa
ምስል AP

እጅጋየሁ ደበበ የ 23 አመት ወጣት ናት። በሴቶች ላይ የሚደርሱ ችግሮች ለሌሎች እህቶቼ ላካፍል እፈልጋለሁ ስትል ወደ ዶይቸ ቬለ መልዕክት ላከችልን። በስልክ አነጋግረናታል። እንደ በርካታ ሴት ኢትዮጵያውያን እጅጋየውን ከሀገሯ እንድትወጣ የዳረጋት ችግር ነው። አጀማመሬ ጥሩ ነበር ትላለች። በአርሲ ስሬ ወረዳ እስከ 10ኛ ክፍል ትምህርቷን ተከታተለች። ኋላም ቀጥላ ለመማር የትምህርት ነጥቧ ጥሩ ስላልነበር፤ ወደ ደብረዘይት ከተማ እህቷ ጋ ሄደች። ወደ ሳውዲ እስክትሄድ ድረስ እዛም ስትሰራ እና ስትማር ቆየች።

ውጪ የሚኖሩ ሰዎች አብዛኛውን ጊዜ የራሳቸውን እና የቤተሰባቸውን ህይወት ሲለውጡ ይታያል። ከበስተ ጀርባ ያለው ታሪክ ግን ሌላ ነው ትላለች ወጣቷ፤ በሷ እና በሌሎች ሴቶች ላይ የደረሱ የመድፈር ሙከራዎች በግልፅ አጫውታናለች።

እጅጋየሁ ኢትዮጵያ ሳለች በፅዳት ሰራተኝነት 400 ብር ፤ ሳውዲ አረቢያ ደግሞ 3500 ብር ታገኛለች ። ሲከፋት እና ስታዝን፤ ስሜቷን በግጥም ነበር ከዚህ ቀደም የምትገልፀው።

በአረብ ሀገር ህይወት ከባድ ከሆነ፤ ለምን ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ እንዳልሞከረችም ነግራናለች። ከዘገባው ያገኙታል።

ልደት አበበ

ሒሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ