1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ወጣት እናቶችና የኑሮ ውድነት በኢትዮጵያ

ዓርብ፣ ሚያዝያ 26 2004

የዛሬው የወጣቶች ዓለም መሰናዶ ርዕስ «ልጆቻቸውን ለብቻቸው የሚያሳድጉ ወጣት እናቶች እና የኑሮ ውድነት በኢትዮጵያ» የሚል ነው። ከአዲስ አበባ እና ከኢልባቡር ሁለት ወጣት እናቶችን አነጋግረናል። የስራ ውሎው፣ ልጅ የማሳደጉ፣ የኑሮ ውድነቱ እና የማኅበራዊ ህይወት መስተጋብሩ በወጣቶቹ ዘንድ ምን ይመስላል? ከራሳቸው ከወጣቶቹ አንደበት እንሰማለን።

https://p.dw.com/p/14pK7
ምስል picture alliance/dpa

የዛሬው የወጣቶች ዓለም መሰናዶ ርዕስ «ልጆቻቸውን ለብቻቸው የሚያሳድጉ ወጣት እናቶች እና የኑሮ ውድነት በኢትዮጵያ» የሚል ነው። ከአዲስ አበባ እና ከኢልባቡር ሁለት ወጣት እናቶችን አነጋግረናል። የስራ ውሎው፣ ልጅ የማሳደጉ፣ የኑሮ ውድነቱ እና የማኅበራዊ ህይወት መስተጋብሩ በወጣቶቹ ዘንድ ምን ይመስላል? ከራሳቸው ከወጣቶቹ አንደበት እንሰማለን።

ልጆቻቸውን በተለያየ ምክንያት ለብቻቸው የሚያሳድጉ እናቶች ቁጥር በኢትዮጵያ በውል ባይታወቅም በርካታ እንደሆኑ ግን ብዙዎች ይገመታሉ። በተለይ እናቶቹ ወጣት በሚሆኑበት ጊዜ የሚያጋጥማቸው ፈተና እና የኑሮ ውጣ ውረድ እንዲህ በቀላሉ የሚገለፅ አይደለም። የሃያ ስድስት ዓመቷ ወጣት ነፃነት ታከለ ነዋሪነቷ በአዲስ አበባ ከተማ ነው። በቅርቡ አራት ዓመት የሚሞላት ልጇን ለብቻዋ ማሳደግ የጀመረችው የሃያ ሶስት ዓመት ወጣት ሳለች አንስቶ ነው።

የሃያ አራት ዓመት ወጣቷ ትዕግስት ወንድሙ ደግሞ በሙያዋ መምህርት ናት። ኢልባቡር መቱ በሚገኝ የገጠር ትምህርት ቤት ውስጥ ነው የምታስተምረው። የአንድ ልጅ እናት ስትሆን በስራ ምክንያት ከባለቤቷ ርቃ መኖር ከጀመረች ዓመታት ተቆጥረዋል። በወጣትነት ለብቻ ልጅ የማሳደጉን ከባድ ፈተና እንደምንም እየተወጣችው እንደሆነ ነው የምትገልፀው።

በእርግጥ የኑሮ ውድነቱ ተፅዕኖውን ያሳረፈው ልጆቻቸውን ለብቻቸው በሚያሳድጉ ወጣት እናቶች ላይ ብቻ ሳይሆን፤ በአብዛኛው ኅብረተሰብም እንደሆነ እየተገለፀ ነው። በተለይ በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ የመጣው የዋጋ ግሽበት ያስከተለው የኑሮ ውድነት በርካቶችን ለችግር መዳረጉ ይታወቃል። ወጣቷ መምህርት ትዕግስት ወንድሙ፥

ጉዳዩ የሚመለከተው መስሪያ ቤት ባወጣው ዘገባ የዋጋ ግሽበቱ 32.5 በመቶ እንደሆነ ገልጿል። ይህ መረጃ እንግዲህ ከመንግስት በኩል የተገኘ ሲሆን፤ አንዳንዶች ግሽበቱ ከዚያም በላይ እንደሆነ ነው የሚጠቁሙት። እንደ ገለፃው የምግብ ዋጋ ብቻውን በኢትዮጵያ የዘንድሮው ከዓምናው የመጋቢት ወር ጋር ሲነፃፀር በ40.9 ያህል ማሻቀቡ ይታወቃል። ተፅዕኖው እንደ አብዛኛው ኅብረተሰብ ወጣት ነፃነትን የሚመለከት ይሆን?

የኑሮ ውድነት ኢትዮጵያ ውስጥ በማኅበረሰቡ ዘንድ ያሳደረውን ተፅዕኖ ለአብነት ያህል ለማሳየት አዲስ አበባ እና ኢልባቡር የሚኖሩ ሁለት ወጣቶችን ያቀረብንበት ዝግጅት ነበር። «ልጆቻቸውን ለብቻቸው የሚያሳድጉ ወጣት እናቶች እና የኑሮ ውድነት በኢትዮጵያ» በሚል ያጠናቀርነው ዝግጅት በዚህ ይጠናቀቃል።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ሒሩት መለስ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ