የኢትዮጵያ የጉዞ አቅጣጫ
ሰኞ፣ ጥቅምት 14 2009ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ የፖለቲካ ቀውስ እና መፍትሄው ላይ ያተኮረ ጉባኤ ዋሽንግተን ዲሲ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ተካሂዷል። ትናንት እና ከትናንት በስተያ የተካሄደው ይኽው ጉባኤ በኢትዮጵያ የወደፊት የጉዞ አቅጣጫ እንዲሁም ሀገሪቱ ምን ዓይነት ሽግግር ማድረግ አለባት በሚሉ ነጥቦችም ላይ ተነጋግሯል። በጉባኤው ላይ የእምነት ተቋማት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ እና የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ተወካዮች ተገኝተዋል። የዋሽንግተን ዲሲው ዘጋቢያችን ዝርዝሩን ልኮልናል።
መክብብ ሸዋ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ