ዓለም ዓቀፍ ቀይመስቀል እና አፍሪቃ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 20 2003ማስታወቂያ
ሰብዓዊ ቀዉስ እንደታየበት በሚነገረዉ የሊቢያ ግጭትና ጦርነት ጉዳይ ለመነጋገር አዲስ አበባ እንደሚገኙ ከአዲስ አበባ ወኪላችን ታደሰ እንግዳዉ በላከልን ዘገባ አመልክቷል። ዛሬ ከአፍሪቃ ኅብረት ባለስልጣናት ጋ እንደሚነጋገሩ የሚጠበቀዉ ኬለንበርገር ትናንት ከኢትዮጵያዉ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጋር በተለያዩ የጋራ ጉዳዮች ላይ መምከራቸዉን ዘገባዉ ጨምሮ ገልጿል። የዓለም ዓቀፉ ቀይ መስቀል ፕሬዝደንት በአዲስ አበባ ከሰነበቱት የሊቢያ ተቃዋሚ ኃይሎች ጋ በተለያየ ጊዜ መምከራቸዉን የገለፁ ሲሆን በተለይ በሚስራታ ያለዉ ሰብዓዊ ቀዉስ እጅግ አሳሳቢ እንደሆነ መጠቆማቸዉን የወኪላችን ዘገባ ያስረዳል።
ዝርዝር ዘገባዉ እነሆ!
ታደሰ እንግዳዉ
ሸዋዬ ለገሠ
ተክሌ የኋላ