1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዓመታዊው የጋዜጠኞችን ፍዳ የዳሰሰው መግለጫ፣

ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 9 2006

በፓሪስና በኒው ዮርክ የሚገኙት ፣ ድንበር አያግዴው የጋዜጠኞች ድርጅት (RSF) እና ለጋዜጠኞች ህልውናና መብት ተሟጋቹ ፤ (CPJ)፣ በዓለም ዙሪያ የጋዜጠኞችን ፍዳ የሚዘረዝረውን ዓመታዊ መግለጫቸውን ይፋ አደረጉ። ለመገባደድ 2 ሳምንት ገደማ በቀረው 2013 ጎርጎሪዮሳዊው ዓመት

https://p.dw.com/p/1AcE6

ውስጥ 71 ጋዜጠኞች መገደላቸውናና 178 በእሥራት በመማቀቅ ላይ እንደሚገኙ የወጣው ዘገባ ያስረዳል። ጋዜጠኞችን አሥሮ በማሠቃየት ከተወቁት 10 ሃገራት መካከል፤ ኤርትራ ፣ ኢትዮጵያ፤ግብፅ ፣ ቪየትናም፤ ሶሪያ ፤ አዘርባጃንና ዑዝቤኪስታን ይገኙበታል። በአፍሪቃው ቀንድ የጋዜጠኞችን ይዞታ የሚከታተሉትን ፤ በምሥራቅ አፍሪቃ የ CPJ ን ተጠሪ በማነጋገር ፤ ተከታዩን ዘገባ አቅርበናል።

Mediendialog Nairobi 2013
ምስል DW/C. Hauswedell

በሥራ ላይ እንዳሉ ጋዜጠኞች ሕይወታቸውን ያጡባቸው አካባቢዎች ፤ እስያ፤ (24 ናቸው የተገደሉት፤)መካከለኛው ምሥራቅና ሰሜን አፍሪቃ (23) ከሰሐራ ምድረ በዳ በስተደቡብ በሚገኙ የአፍሪቃ ሃገራት አምና 21 እንደተገደሉ ሲታወቅ ዘንድሮ ከሞላ ጎደል በግማሽ ቀንሶ (10) ጋዜጠኞች ናቸው ሕይወታቸውን የገበሩት። ግድያው በአመዛኙ ፍልሚያ በሚካሄድባት ሶማልያ ነው የተፈጸመው። አምና 18 ፤ ዘንድሮ 7!

በአፍሪቃው ቀንድ ፤ በእሥራት የሚማቅቁት ቁጥር ቀላል አይደለም። ስለሆነም CPJ ቢ,ታሠሩ ጋዜጠኞች እንዲለቀቁ ከመጠየቅ አልቦዘነም፣ የአፍሪቃውን ቀንድ፤ በተለይ የኢትዮጵያ ን የኤርትራንና የጂቡቲን ጋዜጠኞች ይዞታ እንዴት እንደሚገመግሙት ፤ የ CPJ ውን ተወካይ ቶም ሮደስን በስልክ ጠይቄአቸው ነበር።

«ሂደቱ ፤ አዝማሚያው ፤ የሚያሳዝን ነው፤ አለመታደል ሆኖ ባለፉት ዓመታት የታዘብነው ነው እንደቀጠለ ያለው። ከሰሐራ በስተደቡብ በሚገኙ አገሮችን አያያዝ፣ በዛ ያሉ ጋዜጠኞች የመታሠራቸው ጉዳይ የአፍሪቃው ቀንድ ይዞታ ፤ የአፍሪቃ ሕብረት አያኢዝ ተምሳሌት ነው።»

CPJ, RSF, እና የሰብአዊ መብት ድርጅቶች፣ AI ,HRW ስለጋዜጠኞችም ሆነ በአጠቃላይ ስለሰብአዊ መብትና የፕረስ ነጻነት እንደሚቆረቆሩ የሚሰማ ጉዳይ ነው። ተሰሚነት ያላቸው እዚህ ላይ አንዳንድ ምዕራባውያን መንግሥታት ፣ ምን ማድረግ ይኖርባቸዋል ይላሉ?

Symbolbild Journalismus TV Online
ምስል Fotolia/PinkShot

«ጥሩ ጥያቄ ነው ያነሣህ፤ ግን ጥሩ መልስ አላገኝልህም። ልክ ነህ፤ CPJ ፤ RSF እና ሌሎች ያለማቋረጥ፤ ብዙዎች ጋዜጠኞች መታሠራቸውን እናወግዛለን። የወረበባቸውንም ክስ አጠያያቂ አድረገን ነው የምንመለከተው። ለምሳሌ የኤርትራውን ብትመለከት፣ በ 22 የክስ አንቀጾች የተከሰሱት ሰዎች ጉዳይ ሲመረመር ፣ አንዳችም ፍርድ ቤት ክስ አልተመሠረተባቸውም። እነዚህን መንግስታት በተቻለ መጠን እንሟገታቸዋለን።

ህጋዊ ምርመራ እንዲካሄድ እንደጠይቃለን፤ ለምሳሌ በኢትዮጵያ የተደረገው ዓይነት ማለት ነው፤---። ግን ይህ በቂ አይመስለኝም። በመጨረሻ ፍትሕ እንዲያገኙ ማድረግ ይጠበቅናል። ብዙዎች፤ በሚያሠቅቅ ሁኔታ ነው እሥር ቤት ውስጥ የሚገNUት። ታሣሪዎቹ ጋዜጠኞች፤ ሊፈቱ በሚችሉበት ተስማሚ መፍትኄ ከመንግሥት ጋር ለማግኘት ከዚህ የላቀ ተግባር ማከናወን ይጠበቅብናል።»

ዋና ጽ/ቤቱ በኒውዮርክ የሚገኘው ለጋዜጠኞች ደህንነት የሚታገለው ድርጅት CPJ የአፍሪቃው ቀንድ ጉዳይ ተመልካች ቶም ሮደስ ፤ በደል የፈጸሙ ሰዎች ከመከሰስ ነጻ የሆኑበትን አሠራር እስመልክተው እንዲህ ነበረ ያሉት።

Anschlag Selbstmordanschlag in Nigeria Abuja‎ NO FLASH
ምስል dapd

« CPJ ዘመቻ ከሚያካሂድባቸው ጉዳዮች አንዱ በደል ፈጽሞ በቸልታ መታለፍን ነው። እናም መንግሥታት፤ ያወጡትን ሕግ አክብረው መብት እንዲጠበቅ ያደርጉ ዘንድ ነው የምናስገነዝባቸው። እንደሚመስለኝ፤ችላ መባል ነው፤ በአፍሪቃው ቀንድ ዘገባችን እንደሚያመለክተው ብዙ ጋዜጠኞች እንዲታሠሩ ያደረገው።»

ተክሌ የኋላ

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ